-
በርናባስ “የመጽናናት ልጅ”መጠበቂያ ግንብ—1998 | ሚያዝያ 15
-
-
በ33 እዘአ ከጰንጠቆስጤ በኋላ፣ የቆጵሮስ ሰው የነበረው ሌዋዊው በርናባስ በራሱ ፍላጎት መሬቱን ሸጠና ገንዘቡን ለሐዋርያት ሰጣቸው። ይህንን ያደረገው ለምን ነበር? በሐዋርያት ሥራ ላይ ያለው ዘገባ በዚያን ጊዜ በኢየሩሳሌም ከነበሩት ክርስቲያኖች መሃል “ማናቸውም እንደሚፈልግ መጠን ለእያንዳንዱ ያካፍሉት ነበር” በማለት ይነግረናል። በርናባስ እርዳታ እንደሚያስፈልግ በግልጽ ተገንዝቦ ስለነበር በደግነት ተነሳስቶ በጉዳዩ ላይ አንድ ነገር አደረገ። (ሥራ 4:34-37) በርናባስ ጥሩ ኑሮ የነበረው ሊሆን ቢችልም የአምላክን መንግሥት ለማስቀደም ሲል ቁሳዊ ሀብቱንም ሆነ ራሱን ለማቅረብ ወደ ኋላ አላለም።b ኤፍ ኤፍ ብሩስ የተባሉ ሃይማኖታዊ ምሁር እንደተገነዘቡት “በርናባስ ማበረታቻ የሚያስፈልጋቸው ሰዎችም ሆኑ ማበረታቻ የሚጠይቁ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙት የሚችለውን ያህል ከማበረታታት ወደ ኋላ አይልም ነበር።” ይህንን ሁኔታ እሱ ለሁለተኛ ጊዜ ከተጠቀሰበት ታሪክ በግልጽ ማየት ይቻላል።
-
-
በርናባስ “የመጽናናት ልጅ”መጠበቂያ ግንብ—1998 | ሚያዝያ 15
-
-
b አንዳንዶች የሙሴ ሕግ የሚደነግገውን መሠረት በማድረግ በርናባስ ሌዋዊ ሆኖ ሳለ እንዴት የራሱ መሬት ሊኖረው ቻለ በማለት ይጠይቃሉ። (ዘኁልቁ 18:20) ይሁን እንጂ መሬቱ የሚገኘው በፍልስጤም ይሁን በቆጵሮስ ግልጽ እንዳልሆነ መታወስ አለበት። በተጨማሪም በርናባስ በኢየሩሳሌም አካባቢ በውርስ ያገኘው የመቃብር ቦታም ሊሆን ይችላል። ያም ሆነ ይህ በርናባስ ሌሎችን ለመርዳት ሲል መሬቱን ሸጧል።
-