መዝሙር
የቆሬ ልጆች+ መዝሙር። ማህሌት።
87 የአምላክ ከተማ የተመሠረተችው በተቀደሱት ተራሮች ላይ ነው።+
2 ይሖዋ ከያዕቆብ ድንኳኖች ሁሉ ይበልጥ
የጽዮንን በሮች ይወዳል።+
3 የእውነተኛው አምላክ ከተማ ሆይ፣ ስለ አንቺ አስደናቂ የሆኑ ነገሮች እየተነገሩ ነው።+ (ሴላ)
እንዲህም ይባላል፦ “ይህ በዚያ የተወለደ ነው።”
5 ስለ ጽዮን ደግሞ እንዲህ ይባላል፦
“ይሄኛውም ሆነ ያኛው የተወለደው በእሷ ውስጥ ነው።”
ልዑሉ አምላክም አጽንቶ ይመሠርታታል።
6 ይሖዋ ሕዝቡን ሲመዘግብ
“ይህ በዚያ የተወለደ ነው” ብሎ ያስታውቃል። (ሴላ)