የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘፍጥረት 38
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ዘፍጥረት የመጽሐፉ ይዘት

      • ይሁዳና ትዕማር (1-30)

ዘፍጥረት 38:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 24:2, 3፤ 28:1

ዘፍጥረት 38:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 26:19

ዘፍጥረት 38:5

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ይሁዳን ያመለክታል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢያሱ 19:29, 31

ዘፍጥረት 38:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ማቴ 1:3

ዘፍጥረት 38:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 25:5, 6፤ ማቴ 22:24

ዘፍጥረት 38:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሩት 4:6
  • +ዘዳ 25:7, 9

ዘፍጥረት 38:10

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ዜና 2:3

ዘፍጥረት 38:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 26:19

ዘፍጥረት 38:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 38:2
  • +ዘፍ 38:1
  • +ኢያሱ 15:10, 12፤ መሳ 14:1

ዘፍጥረት 38:14

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 25:5

ዘፍጥረት 38:16

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 38:11

ዘፍጥረት 38:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 41:42፤ 1ነገ 21:8

ዘፍጥረት 38:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 38:1

ዘፍጥረት 38:24

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 21:9

ዘፍጥረት 38:25

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 38:16, 18

ዘፍጥረት 38:26

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 38:11፤ ዘዳ 25:5

ዘፍጥረት 38:29

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “መጣስ” የሚል ትርጉም አለው፤ ማህፀኗን ጥሶ መውጣቱን የሚያመለክት ሳይሆን አይቀርም።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 46:12፤ ሩት 4:12፤ 1ዜና 2:4፤ ሉቃስ 3:23, 33

ዘፍጥረት 38:30

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ማቴ 1:3

ተዛማጅ ሐሳብ

ዘፍ. 38:2ዘፍ 24:2, 3፤ 28:1
ዘፍ. 38:3ዘኁ 26:19
ዘፍ. 38:5ኢያሱ 19:29, 31
ዘፍ. 38:6ማቴ 1:3
ዘፍ. 38:8ዘዳ 25:5, 6፤ ማቴ 22:24
ዘፍ. 38:9ሩት 4:6
ዘፍ. 38:9ዘዳ 25:7, 9
ዘፍ. 38:101ዜና 2:3
ዘፍ. 38:11ዘኁ 26:19
ዘፍ. 38:12ዘፍ 38:2
ዘፍ. 38:12ዘፍ 38:1
ዘፍ. 38:12ኢያሱ 15:10, 12፤ መሳ 14:1
ዘፍ. 38:14ዘዳ 25:5
ዘፍ. 38:16ዘፍ 38:11
ዘፍ. 38:18ዘፍ 41:42፤ 1ነገ 21:8
ዘፍ. 38:20ዘፍ 38:1
ዘፍ. 38:24ዘሌ 21:9
ዘፍ. 38:25ዘፍ 38:16, 18
ዘፍ. 38:26ዘፍ 38:11፤ ዘዳ 25:5
ዘፍ. 38:29ዘፍ 46:12፤ ሩት 4:12፤ 1ዜና 2:4፤ ሉቃስ 3:23, 33
ዘፍ. 38:30ማቴ 1:3
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ዘፍጥረት 38:1-30

ዘፍጥረት

38 በዚሁ ጊዜ አካባቢ ይሁዳ ከወንድሞቹ ተለይቶ በመውረድ ሂራ በሚባል አዱላማዊ ሰው አቅራቢያ ድንኳኑን ተከለ። 2 በዚያም ሹአ የሚባል የአንድ ከነአናዊ ሰው ሴት ልጅ+ አየ። እሷንም አገባትና ከእሷ ጋር ግንኙነት ፈጸመ፤ 3 እሷም ፀነሰች። ወንድ ልጅም ወለደች፤ ስሙንም ኤር+ አለው። 4 ዳግመኛም ፀነሰች፤ ወንድ ልጅም ወለደች፤ ስሙንም ኦናን አለችው። 5 በድጋሚም ሌላ ወንድ ልጅ ወለደች፤ ስሙንም ሴሎም አለችው። እሱም* ልጅ በወለደችለት ጊዜ አክዚብ+ በሚባል ቦታ ነበር።

6 ከጊዜ በኋላ ይሁዳ ለበኩር ልጁ ለኤር ሚስት አመጣለት፤ ስሟም ትዕማር+ ይባል ነበር። 7 ይሁንና የይሁዳ የበኩር ልጅ ኤር ይሖዋ ያዘነበት ሰው ነበር፤ በመሆኑም ይሖዋ በሞት ቀሰፈው። 8 በዚህ የተነሳ ይሁዳ ኦናንን “ከወንድምህ ሚስት ጋር ግንኙነት በመፈጸም የዋርሳነት ግዴታህን ተወጣ፤ ለወንድምህም ዘር ተካለት” አለው።+ 9 ኦናን ግን የሚወለደው ልጅ የእሱ ልጅ እንደሆነ ተደርጎ እንደማይቆጠር ያውቅ ነበር።+ በመሆኑም ለወንድሙ ዘር ላለመተካት ሲል ከወንድሙ ሚስት ጋር ግንኙነት በሚፈጽምበት ጊዜ ዘሩን መሬት ላይ ያፈስ ነበር።+ 10 እሱም ያደረገው ነገር በይሖዋ ፊት መጥፎ ስለነበር አምላክ በሞት ቀሰፈው።+ 11 ይሁዳ ምራቱን ትዕማርን “ልጄ ሴሎም እስኪያድግ ድረስ በአባትሽ ቤት መበለት ሆነሽ ተቀመጪ” አላት፤ ይህን ያላት ‘እሱም እንደ ወንድሞቹ ሊሞትብኝ ይችላል’ ብሎ ስላሰበ ነው።+ ስለዚህ ትዕማር ሄዳ በአባቷ ቤት መኖር ጀመረች።

12 የተወሰነ ጊዜ ካለፈ በኋላም የሹአ+ ልጅ የሆነችው የይሁዳ ሚስት ሞተች። ይሁዳም ሐዘን ተቀምጦ ተነሳ፤ ከዚያም ከአዱላማዊው ወዳጁ ከሂራ+ ጋር በመሆን በጎቹን የሚሸልቱለት ሰዎች ወዳሉበት ወደ ቲምና+ ሄደ። 13 ትዕማርም “አማትሽ በጎቹን ለመሸለት ወደ ቲምና እየወጣ ነው” ተብሎ ተነገራት። 14 በዚህ ጊዜ የመበለትነት ልብሷን በማውለቅ የአንገት ልብስ ተከናንባና ፊቷን ተሸፍና ወደ ቲምና በሚወስደው መንገድ ላይ በምትገኘው በኤናይም መግቢያ ላይ ተቀመጠች፤ ይህን ያደረገችው ሴሎም ቢያድግም ለእሱ እንዳልተዳረች ስላየች ነው።+

15 ይሁዳም ባያት ጊዜ ዝሙት አዳሪ መሰለችው፤ ምክንያቱም ፊቷን ሸፍና ነበር። 16 ስለሆነም ከመንገዱ ወጣ በማለት ወደ እሷ ጠጋ ብሎ “እባክሽ አብሬሽ እንድተኛ ፍቀጂልኝ” አላት፤ ይህን ያደረገውም ምራቱ መሆኗን ስላላወቀ ነው።+ ሆኖም እሷ “አብሬህ ብተኛ ምን ትሰጠኛለህ?” አለችው። 17 እሱም “ከመንጋዬ መካከል አንድ የፍየል ጠቦት እልክልሻለሁ” አላት። እሷ ግን “ጠቦቱን እስክትልክልኝ ድረስ መያዣ ትሰጠኛለህ?” አለችው። 18 እሱም “ምን መያዣ ልስጥሽ?” አላት። እሷም “የማኅተም ቀለበትህን+ ከነማንጠልጠያ ክሩ እንዲሁም በእጅህ የያዝከውን በትርህን ስጠኝ” አለችው። ከዚያም እነዚህን ነገሮች ሰጣት፤ ከእሷም ጋር ተኛ፤ ከእሱም ፀነሰች። 19 ከዚያ በኋላ ተነስታ ሄደች፤ የአንገት ልብሷንም አውልቃ የመበለትነት ልብሷን ለበሰች።

20 ይሁዳም መያዣውን ከሴቲቱ እጅ ለማስመለስ አዱላማዊ+ ወዳጁን የፍየል ጠቦት አስይዞ ወደ እሷ ላከው፤ እሱ ግን ፈጽሞ ሊያገኛት አልቻለም። 21 እሱም የአካባቢውን ሰዎች “ያቺ መንገድ ዳር የምትቀመጠው በኤናይም ያለች የቤተ መቅደስ ዝሙት አዳሪ የት አለች?” በማለት ጠየቀ። እነሱ ግን “ኧረ በዚህ አካባቢ የቤተ መቅደስ ዝሙት አዳሪ ታይታ አትታወቅም” አሉት። 22 በመጨረሻም ወደ ይሁዳ ተመልሶ እንዲህ አለው፦ “ሴቲቱን በፍጹም ላገኛት አልቻልኩም፤ ደግሞም የአካባቢው ሰዎች ‘በዚህ አካባቢ የቤተ መቅደስ ዝሙት አዳሪ ታይታ አትታወቅም’ አሉኝ።” 23 በመሆኑም ይሁዳ “በኋላ እኛ መሳለቂያ እንዳንሆን መያዣውን ትውሰደው። እኔ እንደሆነ ይህን ጠቦት ልኬላት ነበር፤ አንተ ግን ፈጽሞ ልታገኛት አልቻልክም” አለው።

24 ይሁን እንጂ ከሦስት ወር በኋላ ለይሁዳ “ምራትህ ትዕማር ዝሙት አዳሪ ሆናለች፤ ዝሙት በመፈጸሟም ፀንሳለች” ተብሎ ተነገረው። በዚህ ጊዜ ይሁዳ “አውጧትና በእሳት ትቃጠል” አለ።+ 25 እሷም ይዘዋት እየሄዱ ሳሉ ለአማቷ “የፀነስኩት የእነዚህ ዕቃዎች ባለቤት ከሆነ ሰው ነው” የሚል መልእክት ላከችበት። በተጨማሪም “ይህ የማኅተም ቀለበትና ማንጠልጠያ ክሩ እንዲሁም ይህ በትር የማን እንደሆነ እስቲ አጣራ” አለችው።+ 26 ይሁዳም ዕቃዎቹን ከተመለከተ በኋላ “እሷ ከእኔ ይልቅ ጻድቅ ናት፤ ምክንያቱም ለልጄ ለሴሎም ልድራት ይገባኝ ነበር” አለ።+ ከእሷም ጋር ዳግመኛ የፆታ ግንኙነት አልፈጸመም።

27 የመውለጃዋም ጊዜ ሲደርስ በሆዷ ውስጥ መንታ ልጆች እንዳሉ ታወቀ። 28 በምትወልድበት ጊዜም አንደኛው ልጅ እጁን አወጣ፤ አዋላጇም “መጀመሪያ የወጣው ይህ ነው” በማለት ወዲያውኑ በእጁ ላይ ቀይ ክር አሰረችለት። 29 ይሁን እንጂ ልጁ እጁን በመለሰ ጊዜ ወንድሙ ቀድሞት ወጣ፤ በመሆኑም አዋላጇ “አንተ እንዴት ጥሰህ ወጣህ?” አለች። በመሆኑም ስሙ ፋሬስ*+ ተባለ። 30 በኋላም እጁ ላይ ቀይ ክር የታሰረለት ወንድሙ ወጣ፤ ስሙም ዛራ+ ተባለ።

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ