የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘፍጥረት 37
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ዘፍጥረት የመጽሐፉ ይዘት

      • የዮሴፍ ሕልሞች (1-11)

      • ዮሴፍና ቅናት ያደረባቸው ወንድሞቹ (12-24)

      • ዮሴፍ ለባርነት ተሸጠ (25-36)

ዘፍጥረት 37:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 23:3, 4፤ 28:1, 4፤ ዕብ 11:8, 9

ዘፍጥረት 37:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 30:25፤ 46:19
  • +ዘፍ 35:25, 26
  • +ዘፍ 47:3

ዘፍጥረት 37:3

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “የሚያምር ረጅም ልብስ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ዜና 2:1, 2

ዘፍጥረት 37:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 37:19

ዘፍጥረት 37:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:6, 9

ዘፍጥረት 37:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 45:8፤ 49:26

ዘፍጥረት 37:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 44:14፤ 45:9

ዘፍጥረት 37:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሥራ 7:9

ዘፍጥረት 37:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 33:18

ዘፍጥረት 37:14

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ረባዳማ ሜዳ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 23:19፤ 35:27

ዘፍጥረት 37:19

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 37:5

ዘፍጥረት 37:21

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሱን።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 49:3
  • +ዘፍ 9:5፤ ዘፀ 20:13

ዘፍጥረት 37:22

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “እጃችሁን አታሳርፉበት።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 4:8, 10፤ 42:22
  • +ዘፍ 42:21

ዘፍጥረት 37:23

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 37:3

ዘፍጥረት 37:25

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 25:12
  • +ዘፍ 43:11

ዘፍጥረት 37:26

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 4:8, 10

ዘፍጥረት 37:27

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሥራ 7:9

ዘፍጥረት 37:28

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 25:1, 2
  • +ዘፍ 40:15፤ 45:4፤ መዝ 105:17

ዘፍጥረት 37:32

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 37:3

ዘፍጥረት 37:35

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ሲኦል።” የሰው ልጆችን ሁሉ መቃብር ያመለክታል። የቃላት መፍቻውን ተመልከት።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:38፤ 44:29፤ መዝ 89:48፤ መክ 9:10፤ ሆሴዕ 13:14፤ ሥራ 2:27፤ ራእይ 20:13

ዘፍጥረት 37:36

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 39:1
  • +ዘፍ 40:2, 3

ተዛማጅ ሐሳብ

ዘፍ. 37:1ዘፍ 23:3, 4፤ 28:1, 4፤ ዕብ 11:8, 9
ዘፍ. 37:2ዘፍ 30:25፤ 46:19
ዘፍ. 37:2ዘፍ 35:25, 26
ዘፍ. 37:2ዘፍ 47:3
ዘፍ. 37:31ዜና 2:1, 2
ዘፍ. 37:5ዘፍ 37:19
ዘፍ. 37:7ዘፍ 42:6, 9
ዘፍ. 37:8ዘፍ 45:8፤ 49:26
ዘፍ. 37:9ዘፍ 44:14፤ 45:9
ዘፍ. 37:11ሥራ 7:9
ዘፍ. 37:12ዘፍ 33:18
ዘፍ. 37:14ዘፍ 23:19፤ 35:27
ዘፍ. 37:19ዘፍ 37:5
ዘፍ. 37:21ዘፍ 49:3
ዘፍ. 37:21ዘፍ 9:5፤ ዘፀ 20:13
ዘፍ. 37:22ዘፍ 4:8, 10፤ 42:22
ዘፍ. 37:22ዘፍ 42:21
ዘፍ. 37:23ዘፍ 37:3
ዘፍ. 37:25ዘፍ 25:12
ዘፍ. 37:25ዘፍ 43:11
ዘፍ. 37:26ዘፍ 4:8, 10
ዘፍ. 37:27ሥራ 7:9
ዘፍ. 37:28ዘፍ 25:1, 2
ዘፍ. 37:28ዘፍ 40:15፤ 45:4፤ መዝ 105:17
ዘፍ. 37:32ዘፍ 37:3
ዘፍ. 37:35ዘፍ 42:38፤ 44:29፤ መዝ 89:48፤ መክ 9:10፤ ሆሴዕ 13:14፤ ሥራ 2:27፤ ራእይ 20:13
ዘፍ. 37:36ዘፍ 39:1
ዘፍ. 37:36ዘፍ 40:2, 3
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
  • 31
  • 32
  • 33
  • 34
  • 35
  • 36
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ዘፍጥረት 37:1-36

ዘፍጥረት

37 ያዕቆብ አባቱ የባዕድ አገር ሰው ሆኖ ይኖርበት በነበረው በከነአን ምድር ኖረ።+

2 የያዕቆብ ታሪክ ይህ ነው።

ዮሴፍ+ የ17 ዓመት ወጣት ሳለ ከአባቱ ሚስቶች ከባላና ከዚልጳ ወንዶች ልጆች+ ጋር በጎች ይጠብቅ+ ነበር። እሱም ስለ ወንድሞቹ መጥፎ ድርጊት የሚገልጽ ወሬ ለአባታቸው ይዞለት መጣ። 3 እስራኤል ዮሴፍን የወለደው በስተርጅናው ስለነበር ከሌሎቹ ወንዶች ልጆቹ ሁሉ+ ይበልጥ ይወደው ነበር፤ ለእሱም ልዩ የሆነ ቀሚስ* አሠራለት። 4 ወንድሞቹም አባታቸው ከእነሱ አስበልጦ እንደሚወደው ሲያዩ ይጠሉት ጀመር፤ በሰላምም ሊያናግሩት አልቻሉም።

5 በኋላም ዮሴፍ ሕልም አለመ፤ ሕልሙንም ለወንድሞቹ ነገራቸው፤+ እነሱም እሱን የሚጠሉበት ተጨማሪ ምክንያት አገኙ። 6 እሱም እንዲህ አላቸው፦ “እባካችሁ ያየሁትን ሕልም ልንገራችሁ፣ ስሙኝ። 7 በእርሻ መካከል ነዶ እያሰርን ነበር፤ ከዚያም የእኔ ነዶ ተነስታ ቀጥ ብላ ስትቆም የእናንተ ነዶዎች ደግሞ የእኔን ነዶ ከበው ሰገዱላት።”+ 8 ወንድሞቹም “በእኛ ላይ ንጉሥ ልትሆንና ልትገዛን ታስባለህ ማለት ነው?” አሉት።+ በመሆኑም ያየው ሕልምና የተናገረው ነገር እሱን ይበልጥ እንዲጠሉት አደረጋቸው።

9 ከዚያም ሌላ ሕልም አለመ፤ ሕልሙንም ለወንድሞቹ እንዲህ ሲል ነገራቸው፦ “ሌላም ሕልም አለምኩ። አሁን ደግሞ ፀሐይ፣ ጨረቃና 11 ከዋክብት ሲሰግዱልኝ አየሁ።”+ 10 ሕልሙንም ለአባቱና ለወንድሞቹ ነገራቸው፤ አባቱም ገሠጸው፤ እንዲህም አለው፦ “ይህ ያለምከው ሕልም ፍቺ ምንድን ነው? እኔም ሆንኩ እናትህና ወንድሞችህ መጥተን መሬት ላይ ተደፍተን እንድንሰግድልህ ታስባለህ?” 11 ወንድሞቹም ይበልጥ ቀኑበት፤+ አባቱ ግን ነገሩን በልቡ ያዘው።

12 ወንድሞቹ የአባታቸውን መንጋ ለማሰማራት ሴኬም+ አቅራቢያ ወደሚገኝ ቦታ ሄደው ነበር። 13 በኋላም እስራኤል ዮሴፍን “ወንድሞችህ በሴኬም አቅራቢያ መንጎቹን እየጠበቁ እንዳሉ አውቀሃል አይደል? በል ና፣ ወደ እነሱ ልላክህ” አለው። እሱም “እሺ፣ እሄዳለሁ!” አለ። 14 በመሆኑም “እባክህ ሂድና ወንድሞችህ ደህና መሆናቸውን እይ። መንጋውም ደህና መሆኑን እይና መጥተህ ትነግረኛለህ” አለው። በዚህም መሠረት ከኬብሮን+ ሸለቆ* ወደዚያ ላከው፤ ዮሴፍም ወደ ሴኬም ሄደ። 15 በኋላም ዮሴፍ በሜዳ ላይ ሲባዝን አንድ ሰው አገኘው። ሰውየውም “ምን ፈልገህ ነው?” ሲል ጠየቀው። 16 እሱም “ወንድሞቼን እየፈለግኩ ነው። መንጎቹን እየጠበቁ ያሉት የት እንደሆነ እባክህ ንገረኝ” አለው። 17 ሰውየውም “ከዚህ ሄደዋል፤ ምክንያቱም ‘ወደ ዶታን እንሂድ’ ሲባባሉ ሰምቻቸዋለሁ” አለው። ስለዚህ ዮሴፍ ወንድሞቹን ፍለጋ ሄደ፤ ዶታን ላይም አገኛቸው።

18 እነሱም ከሩቅ ሲመጣ ተመለከቱት፤ አጠገባቸውም ከመድረሱ በፊት እሱን እንዴት እንደሚገድሉት ይመካከሩ ጀመር። 19 እነሱም እንዲህ ተባባሉ፦ “ያውና! ያ ሕልም አላሚ መጣ።+ 20 ኑ፣ እንግደለውና ከውኃ ጉድጓዶቹ በአንዱ ውስጥ እንጣለው፤ ከዚያም ኃይለኛ አውሬ በልቶታል እንላለን። እስቲ የሕልሞቹን መጨረሻ እናያለን።” 21 ሮቤል+ ይህን ሲሰማ ከእነሱ ሊያስጥለው አሰበ፤ በመሆኑም “ሕይወቱን* እንኳ አናጥፋ”+ አለ። 22 ከዚያም እንዲህ አላቸው፦ “ደም አታፍስሱ።+ በምድረ በዳ በሚገኘው በዚህ የውኃ ጉድጓድ ውስጥ ጣሉት እንጂ ጉዳት አታድርሱበት።”*+ ይህን ያላቸው ከእነሱ ሊያስጥለውና ወደ አባቱ ሊመልሰው አስቦ ነበር።

23 ዮሴፍ ወደ ወንድሞቹ እንደደረሰም የለበሰውን ያን ልዩ ቀሚስ+ ገፈፉት፤ 24 ወስደውም የውኃ ጉድጓዱ ውስጥ ጣሉት። ጉድጓዱም ባዶ ነበር፤ ውኃም አልነበረበትም።

25 ከዚያም ሊበሉ ተቀመጡ። ቀና ብለው ሲመለከቱም እስማኤላውያን+ ነጋዴዎች ግመሎቻቸውን አግተልትለው ከጊልያድ ሲመጡ አዩ። እነሱም በግመሎቻቸው ላይ ጥሩ መዓዛ ያለው ሙጫ፣ በለሳንና ከርቤ+ ጭነው ወደ ግብፅ እየወረዱ ነበር። 26 በዚህ ጊዜ ይሁዳ ወንድሞቹን እንዲህ አላቸው፦ “ወንድማችንን ብንገድለውና ደሙን ብንሸሽግ ምን እንጠቀማለን?+ 27 ኑ፣ ለእስማኤላውያን እንሽጠው፤+ እጃችንን አንሰንዝርበት። ደግሞም እኮ እሱ ወንድማችን፣ የገዛ ሥጋችን ነው።” እነሱም በወንድማቸው ሐሳብ ተስማሙ። 28 ምድያማውያን+ ነጋዴዎች በአጠገባቸው ሲያልፉም ዮሴፍን ከውኃ ጉድጓዱ አውጥተው በ20 የብር ሰቅል ለእስማኤላውያን ሸጡት።+ እነሱም ዮሴፍን ወደ ግብፅ ወሰዱት።

29 በኋላም ሮቤል ወደ ውኃ ጉድጓዱ ተመልሶ ዮሴፍ በዚያ አለመኖሩን ሲመለከት ልብሱን ቀደደ። 30 ወደ ወንድሞቹም ተመልሶ “ልጁ የለም! እንግዲህ ምንድን ነው የማደርገው?” አላቸው።

31 ስለዚህ የዮሴፍን ቀሚስ ወሰዱ፤ አንድ ፍየል ካረዱ በኋላም ቀሚሱን ደሙ ውስጥ ነከሩት። 32 ከዚያም ያን ልዩ ቀሚስ እንዲህ ከሚል መልእክት ጋር ወደ አባታቸው ላኩት፦ “ይህን አገኘን፤ እባክህ ይህ የልጅህ ቀሚስ መሆን አለመሆኑን እስቲ እየው።”+ 33 እሱም ልብሱን አገላብጦ ካየው በኋላ “ይሄማ የልጄ ቀሚስ ነው! ኃይለኛ አውሬ በልቶት መሆን አለበት! በቃ ዮሴፍን አውሬ ቦጫጭቆታል ማለት ነው!” አለ። 34 ከዚያም ያዕቆብ ልብሱን ቀደደ፤ በወገቡም ላይ ማቅ ታጥቆ ለብዙ ቀናት ለልጁ አለቀሰ። 35 ወንዶችና ሴቶች ልጆቹ ሁሉ ሊያጽናኑት ሞከሩ፤ እሱ ግን ፈጽሞ ሊጽናና አልቻለም፤ “በልጄ ሐዘን እንደተቆራመድኩ ወደ መቃብር* እወርዳለሁ!”+ ይል ነበር። አባቱም ለልጁ ማልቀሱን አላቋረጠም።

36 በዚህ ጊዜ ምድያማውያን ዮሴፍን ግብፅ ውስጥ ጶጢፋር ለተባለ ሰው ሸጡት፤ ይህ ሰው የፈርዖን የቤተ መንግሥት ባለሥልጣንና+ የዘቦች አለቃ+ ነበር።

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ