ኢዮብ
16 ኢዮብ እንዲህ ሲል መለሰ፦
2 “ከዚህ በፊት እንዲህ ያሉ ብዙ ነገሮች ሰምቻለሁ።
ሁላችሁም የምታስጨንቁ አጽናኞች ናችሁ!+
3 ከንቱ* ቃላት ማብቂያ የላቸውም?
እንዲህ ብለህ እንድትመልስ ያነሳሳህ ምንድን ነው?
4 እኔም እንደ እናንተ መናገር እችል ነበር።
5 እንዲህ ከማድረግ ይልቅ በአፌ ቃል አበረታችሁ ነበር፤
የከንፈሮቼም ማጽናኛ ባሳረፋችሁ ነበር።+
6 ብናገር ከሥቃዬ አልገላገልም፤+
ዝም ብልስ ሥቃዬ ምን ያህል ይቀንስልኛል?
8 ደግሞም ያዝከኝ፤ ይህም ምሥክር ሆኖብኛል፤
በመሆኑም ክሳቴ ተነስቶ በፊቴ ይመሠክራል።
9 ቁጣው ቦጫጨቀኝ፤ በጥላቻ ተመለከተኝ።+
ጥርሱን አፋጨብኝ።
ባላጋራዬ በዓይኑ ወጋኝ።+
11 አምላክ ለልጆች አሳልፎ ሰጠኝ፤
በክፉዎችም እጅ ላይ ገፍትሮ ጣለኝ።+
14 እንደ ግንብ ሰንጥቆ ሰነጣጥቆ አፈራረሰኝ፤
እንደ ተዋጊ ተንደርድሮ መጣብኝ።
18 ምድር ሆይ፣ ደሜን አትሸፍኚ!+
ጩኸቴም ማረፊያ ስፍራ አያግኝ!
19 አሁንም እንኳ ምሥክሬ በሰማያት አለ፤
ስለ እኔ መመሥከር የሚችል በከፍታ ቦታዎች ላይ ይገኛል።
21 በሰውና በባልንጀራው መካከል የሚዳኝ እንደሚኖር፣
በሰውና በአምላክ መካከልም የሚዳኝ ይኑር።+
22 የሚቀሩት ዓመታት ጥቂት ናቸውና፤
እኔም በማልመለስበት መንገድ እሄዳለሁ።+