የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘዳግም 32:31
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 31 የእነሱ ዓለት እንደ እኛ ዓለት አይደለም፤+

      ጠላቶቻችንም እንኳ ይህን ተረድተዋል።+

  • መዝሙር 18:31-42
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 31 ደግሞስ ከይሖዋ ሌላ አምላክ ማን ነው?+

      ከአምላካችንስ ሌላ ዓለት ማን ነው?+

      32 ብርታትን የሚያስታጥቀኝ እውነተኛው አምላክ ነው፤+

      መንገዴንም ፍጹም ያደርግልኛል።+

      33 እግሮቼን እንደ ዋልያ እግሮች ያደርጋል፤

      በከፍታ ቦታዎች ላይ ያቆመኛል።+

      34 እጆቼን ለጦርነት ያሠለጥናል፤

      ክንዶቼ የመዳብ ደጋን ማጠፍ ይችላሉ።

      35 የመዳን ጋሻህን ትሰጠኛለህ፤+

      ቀኝ እጅህ ይደግፈኛል፤

      ትሕትናህም ታላቅ ያደርገኛል።+

      36 ለእርምጃዬ መንገዱን ታሰፋልኛለህ፤

      እግሮቼ* አያዳልጣቸውም።+

      37 ጠላቶቼን አሳድጄ እደርስባቸዋለሁ፤

      ተጠራርገው እስኪጠፉ ድረስ ወደ ኋላ አልመለስም።

      38 እንዳያንሰራሩ አድርጌ አደቃቸዋለሁ፤+

      እግሬ ሥር ይወድቃሉ።

      39 ለውጊያው ብርታት ታስታጥቀኛለህ፤

      ጠላቶቼ ሥሬ እንዲወድቁ ታደርጋለህ።+

      40 ጠላቶቼ ከእኔ እንዲሸሹ ታደርጋለህ፤*

      እኔም የሚጠሉኝን አጠፋቸዋለሁ።*+

      41 እርዳታ ለማግኘት ይጮኻሉ፤ ሆኖም የሚያድናቸው የለም፤

      ወደ ይሖዋም ይጮኻሉ፤ እሱ ግን አይመልስላቸውም።

      42 በነፋስ ፊት እንዳለ አቧራ ፈጽሜ አደቃቸዋለሁ፤

      በመንገድ ላይ እንዳለ ጭቃ አውጥቼ እጥላቸዋለሁ።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ