የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • የዚህ ሳምንት
ከሐምሌ 28–ነሐሴ 3
የክርስቲያናዊ ሕይወትና አገልግሎት ስብሰባ አስተዋጽኦ—2025 | ሐምሌ

ከሐምሌ 28–ነሐሴ 3

ምሳሌ 24

መዝሙር 38 እና ጸሎት | የመግቢያ ሐሳብ (1 ደቂቃ)

ከአምላክ ቃል የሚገኝ ውድ ሀብት

1. ለመከራ ወቅት ራሳችሁን አጠናክሩ

(10 ደቂቃ)

እውቀትና ጥበብ አከማቹ (ምሳሌ 24:5፤ w23.07 18 አን. 15)

ተስፋ አስቆራጭ ሁኔታ በሚያጋጥማችሁ ጊዜም ጭምር መንፈሳዊ ልማዳችሁን ይዛችሁ ቀጥሉ (ምሳሌ 24:10፤ w09 12/15 18 አን. 12-13)

መንፈሳዊ ጥንካሬ ከመከራ እንድናገግም ይረዳናል (ምሳሌ 24:16፤ w20.12 15)

ከባድ ሕመም ያለባት አንዲት እህት ከጓደኛዋ ጋር ከቤት ወደ ቤት በደስታ ስታገለግል። ለቤቱ ባለቤት ከታብሌቷ ላይ አንድ ነገር እያሳየቻት ነው።

2. መንፈሳዊ ዕንቁዎች

(10 ደቂቃ)

  • ምሳሌ 24:27—የዚህ ጥቅስ መልእክት ምንድን ነው? (w09 10/15 12)

  • ከዚህ ሳምንት የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ምን መንፈሳዊ ዕንቁዎች አግኝታችኋል?

3. የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ

(4 ደቂቃ) ምሳሌ 24:1-20 (th ጥናት 11)

በአገልግሎት ውጤታማ ለመሆን ተጣጣር

4. ውይይት መጀመር

(2 ደቂቃ) መደበኛ ያልሆነ ምሥክርነት። ምሥክርነት መስጠት ከመቻልህ በፊት ውይይታችሁ ይደመደማል። (lmd ምዕራፍ 2 ነጥብ 4)

5. ውይይት መጀመር

(3 ደቂቃ) ከቤት ወደ ቤት። (lmd ምዕራፍ 3 ነጥብ 4)

6. ውይይት መጀመር

(3 ደቂቃ) የአደባባይ ምሥክርነት። የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ስለምንሰጥበት ዝግጅት ለግለሰቡ ንገረው፤ እንዲሁም የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት የአድራሻ ካርድ ስጠው። (lmd ምዕራፍ 4 ነጥብ 3)

7. ንግግር

(3 ደቂቃ) lmd ተጨማሪ መረጃ ሀ ነጥብ 11—ጭብጥ፦ አምላክ ሐሳቡን ገልጾልናል። (th ጥናት 6)

ክርስቲያናዊ ሕይወት

መዝሙር 99

8. በመከራ ወቅት እርስ በርስ ተረዳዱ

(15 ደቂቃ) ውይይት።

ወረርሽኝ፣ የተፈጥሮ አደጋ፣ ሕዝባዊ ዓመፅ፣ ጦርነት ወይም ስደት ድንገት ሊከሰት ይችላል። እንዲህ ያለ ሁኔታ ሲከሰት በመከራው የተጎዱት ክርስቲያኖች እርስ በርስ ይረዳዳሉ እንዲሁም ይበረታታሉ። ይሁንና መከራው እኛን በቀጥታ ባይነካንም እንኳ በወንድሞቻችን ላይ በደረሰው ነገር በጣም እናዝናለን፤ እንዲሁም እነሱን ለመርዳት አቅማችን የፈቀደውን ሁሉ እናደርጋለን።—1ቆሮ 12:25, 26

ሥዕሎች፦ ወንድሞችና እህቶች የእምነት አጋሮቻቸውን በተለያዩ መንገዶች ሲረዱ። 1. ወንድሞችና እህቶች በተፈጥሮ አደጋ የወደመን የስብሰባ አዳራሽ መልሰው ሲገነቡ። 2. ወንድሞችና እህቶች ከአካባቢዋ ተሰዳ የመጣችን አንዲት እህትና ልጇን በደስታ ሲቀበሉ። 3. አንዲት እህት በስብሰባ አዳራሽ የመዋጮ ሣጥን ውስጥ መዋጮ ስትከት። 4. ወንድሞችና እህቶች በስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ለተጠለሉ የእምነት አጋሮቻቸው መሠረታዊ ነገሮችን ሲያቀርቡ። 5. ፈቃደኛ ሠራተኞች የታሸገ ውኃ ሲያደርሱ። 6. አንድ ወንድም ሲጸልይ።

አንደኛ ነገሥት 13:6ን እና ያዕቆብ 5:16ለን አንብብ። ከዚያም እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦

  • የአምላክ አገልጋዮች ሌሎችን አስመልክቶ የሚያቀርቡት ጸሎት ትልቅ ኃይል አለው የምንለው ለምንድን ነው?

ማርቆስ 12:42-44ን እና 2 ቆሮንቶስ 8:1-4ን አንብብ። ከዚያም እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦

  • የተቸገሩ ወንድሞቻችንን ለመርዳት ለዓለም አቀፉ ሥራ መዋጮ ማድረግ የምንችለው ብዙ ገንዘብ ባይኖረንም እንኳ እንዲህ ከማድረግ ወደኋላ ማለት የሌለብን ለምንድን ነው?

በእገዳ ሥር ያሉ ወንድሞችን ማበረታታት የተባለውን ቪዲዮ አጫውት። ከዚያም የሚከተሉትን ጥያቄዎች ጠይቅ፦

  • ወንድሞች በምሥራቅ አውሮፓ ሥራችን በታገደባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ የእምነት አጋሮቻቸውን ለመርዳት ምን መሥዋዕት ከፍለዋል?

  • በእገዳ ሥር የነበሩት ወንድሞች አንድ ላይ እንድንሰበሰብና እርስ በርስ እንድንበረታታ የተሰጠንን መመሪያ የታዘዙት እንዴት ነው?—ዕብ 10:24, 25

9. የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት

(30 ደቂቃ) lfb ትምህርት 4-5

የመደምደሚያ ሐሳብ (3 ደቂቃ) | መዝሙር 112 እና ጸሎት

የርዕስ ማውጫ
መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2025 | ግንቦት

የጥናት ርዕስ 21፦ ከሐምሌ 28, 2025–ነሐሴ 3, 2025

14 ቋሚ የሆነችውን ከተማ ተጠባበቁ

ሌሎች ርዕሶች

በዚህ እትም ውስጥ ያሉት ሌሎች ርዕሶች

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ