ዘፍጥረት 29:34 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 34 አሁንም ደግሞ ፀነሰች፤ ወንድ ልጅም ወለደች። እሷም “ሦስት ወንዶች ልጆች ስለወለድኩለት አሁን ባሌ ይቀርበኛል” አለች። በዚህም የተነሳ ሌዊ*+ ተባለ። ዘፍጥረት 49:5-7 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 5 “ስምዖንና ሌዊ ወንድማማቾች ናቸው።+ ሰይፎቻቸው የዓመፅ መሣሪያዎች ናቸው።+ 6 ነፍሴ* ሆይ፣ ከእነሱ ጋር አትወዳጂ። ክብሬ ሆይ፣ ከእነሱ ማኅበር ጋር አትተባበር፤ ምክንያቱም በቁጣ ተነሳስተው ሰዎችን ገድለዋል፤+ ደስ ስላላቸውም ብቻ የበሬዎችን ቋንጃ ቆርጠዋል። 7 ቁጣቸው ጨካኝ፣ ንዴታቸውም ምሕረት የለሽ ስለሆነ የተረገመ ይሁን።+ በያዕቆብ ልበትናቸው፤ በእስራኤልም ላሰራጫቸው።+
5 “ስምዖንና ሌዊ ወንድማማቾች ናቸው።+ ሰይፎቻቸው የዓመፅ መሣሪያዎች ናቸው።+ 6 ነፍሴ* ሆይ፣ ከእነሱ ጋር አትወዳጂ። ክብሬ ሆይ፣ ከእነሱ ማኅበር ጋር አትተባበር፤ ምክንያቱም በቁጣ ተነሳስተው ሰዎችን ገድለዋል፤+ ደስ ስላላቸውም ብቻ የበሬዎችን ቋንጃ ቆርጠዋል። 7 ቁጣቸው ጨካኝ፣ ንዴታቸውም ምሕረት የለሽ ስለሆነ የተረገመ ይሁን።+ በያዕቆብ ልበትናቸው፤ በእስራኤልም ላሰራጫቸው።+