-
1 ነገሥት 7:23-26አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
23 ከዚያም ባሕሩን* በቀለጠ ብረት ሠራ።+ ባሕሩ ክብ ቅርጽ የነበረው ሲሆን ከአንዱ ጠርዝ እስከ ሌላኛው ጠርዝ 10 ክንድ፣ ከፍታው ደግሞ 5 ክንድ ነበር፤ መጠነ ዙሪያውም በመለኪያ ገመድ ሲለካ 30 ክንድ ሆነ።+ 24 በባሕሩም ዙሪያ ከጠርዙ ዝቅ ብሎ በእያንዳንዱ ክንድ ላይ በቅል ቅርጽ+ የተሠሩ አሥር ጌጦች ነበሩ፤ ቅሎቹም በሁለት ረድፍ ከባሕሩ ጋር አንድ ወጥ ሆነው ተሠርተው ነበር። 25 ባሕሩ 3ቱ ወደ ሰሜን፣ 3ቱ ወደ ምዕራብ፣ 3ቱ ወደ ደቡብ እንዲሁም 3ቱ ወደ ምሥራቅ አቅጣጫ ፊታቸውን ባደረጉ 12 በሬዎች+ ላይ ተቀምጦ ነበር፤ ባሕሩም ላያቸው ላይ ነበር፤ የሁሉም ሽንጥ ወደ መሃል ገባ ያለ ነበር። 26 የውኃ ማጠራቀሚያው ውፍረት አንድ ጋት* ነበር፤ ጠርዙ የጽዋ ከንፈር ይመስል የነበረ ሲሆን በአበባ ቅርጽ የተሠራ ነበር። የውኃ ማጠራቀሚያውም 2,000 የባዶስ መስፈሪያ* ይይዝ ነበር።
-