ምሳሌ 13:24 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 24 ልጁን በበትር ከመምታት* ወደኋላ የሚል ይጠላዋል፤+የሚወደው ግን ተግቶ* ይገሥጸዋል።+ ምሳሌ 19:18 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 18 ገና ተስፋ ሳለ ልጅህን ገሥጽ፤+ለእሱም ሞት ተጠያቂ አትሁን።*+ ኤፌሶን 6:4 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 4 አባቶች ሆይ፣ ልጆቻችሁን አታስመርሯቸው፤+ ከዚህ ይልቅ በይሖዋ* ተግሣጽና+ ምክር* አሳድጓቸው።+