የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኢሳይያስ 45:1
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 45 ይሖዋ ለቀባው ለቂሮስ+ እንዲህ ይላል፦

      ብሔራትን በፊቱ ለማስገዛት፣+

      ነገሥታትን ትጥቅ ለማስፈታት*

      እንዲሁም የከተማው በሮች እንዳይዘጉ

      መዝጊያዎቹን በፊቱ ለመክፈት ስል

      ቀኝ እጁን ለያዝኩት+ ለቂሮስ፦

  • ኤርምያስ 51:11
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 11 “ፍላጻዎቻችሁን አሹሉ፤+ ክብ የሆኑትን ጋሻዎች አንሱ።*

      ይሖዋ የሜዶናውያንን ነገሥታት መንፈስ አነሳስቷል፤+

      ምክንያቱም ባቢሎንን ለማጥፋት አስቧል።

      ይህ የይሖዋ በቀል ይኸውም ስለ ቤተ መቅደሱ የሚወስደው የበቀል እርምጃ ነውና።

  • ኤርምያስ 51:27, 28
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 27 “በምድሪቱ ላይ ምልክት* አቁሙ።+

      በብሔራት መካከል ቀንደ መለከት ንፉ።

      በእሷ ላይ እንዲዘምቱ ብሔራትን መድቡ።*

      የአራራት፣+ የሚኒ እና የአሽከናዝ መንግሥታት+ እሷን እንዲወጉ ሰብስቧቸው።

      በላይዋም ወታደሮችን የሚመለምል መኮንን ሹሙባት።

      ፈረሶችንም እንደ ኩብኩባ ስደዱባት።

      28 ብሔራትን፣ የሜዶንን+ ነገሥታት፣ ገዢዎቿን፣ የበታች ገዢዎቿን ሁሉና

      በእያንዳንዳቸው ግዛት ሥር ያለውን ምድር ሁሉ

      በእሷ ላይ እንዲዘምቱ መድቧቸው።*

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ