ኢዮብ 36:27, 28 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 27 እሱ የውኃ ጠብታዎችን ወደ ላይ ይስባል፤+ጭጋጉም ወደ ዝናብነት ይለወጣል፤28 ከዚያም ደመናት ያዘንባሉ፤+በሰው ልጆችም ላይ ዶፍ ያወርዳሉ። መዝሙር 135:7 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 7 ደመና* ከምድር ዳርቻዎች ወደ ላይ እንዲወጣ ያደርጋል፤በዝናብ ጊዜ መብረቅን ያበርቃል፤*ነፋሱን ከግምጃ ቤቱ ያወጣል።+