የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • 2 ነገሥት 23:15, 16
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 15 በቤቴል የነበረውንም መሠዊያ ይኸውም እስራኤላውያን ኃጢአት እንዲሠሩ ያደረገው የናባጥ ልጅ ኢዮርብዓም የሠራውን ከፍ ያለ የማምለኪያ ቦታ አፈረሰ።+ ያን መሠዊያና ከፍ ያለ የማምለኪያ ቦታ ካፈረሰ በኋላ ቦታውን አቃጠለው፤ ፈጭቶም አመድ አደረገው፤ የማምለኪያ ግንዱንም* አቃጠለ።+

      16 ኢዮስያስ ዞር ብሎ በተራራው ላይ ያሉትን መቃብሮች ባየ ጊዜ አፅሞቹን ከመቃብሮቹ ውስጥ አስወጥቶ በመሠዊያው ላይ በማቃጠል እነዚህ ነገሮች እንደሚሆኑ አስቀድሞ የተናገረው የእውነተኛው አምላክ ሰው ባወጀው የይሖዋ ቃል መሠረት መሠዊያውን አረከሰ።+

  • 2 ዜና መዋዕል 31:1
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 31 ከዚህ በኋላ በዚያ የተገኙት እስራኤላውያን በሙሉ ወደ ይሁዳ ከተሞች ወጥተው በመላው ይሁዳና ቢንያም እንዲሁም በኤፍሬምና በምናሴ+ የነበሩትን የማምለኪያ ዓምዶች+ ሰባበሩ፤ የማምለኪያ ግንዶቹን*+ ቆረጡ፤ ከፍ ያሉትንም የማምለኪያ ቦታዎችና+ መሠዊያዎቹን+ አፈራረሱ፤ ምንም ያስቀሩት ነገር አልነበረም፤ ከዚህ በኋላ እስራኤላውያን በሙሉ ወደየከተሞቻቸው፣ እያንዳንዳቸውም ወደየርስታቸው ተመለሱ።

  • 2 ዜና መዋዕል 34:1
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 34 ኢዮስያስ+ በነገሠ ጊዜ ዕድሜው ስምንት ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌምም ሆኖ ለ31 ዓመት ገዛ።+

  • 2 ዜና መዋዕል 34:7
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 7 መሠዊያዎችን አፈራረሰ፤ የማምለኪያ ግንዶችንና* የተቀረጹትን ምስሎች+ ሰባብሮ አደቀቃቸው፤ በመላው የእስራኤል ምድር የሚገኙትንም የዕጣን ማጨሻዎች ሰባበረ፤+ ከዚያም ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ።

  • ሆሴዕ 10:2
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    •  2 ልባቸው ግብዝ* ነው፤

      በመሆኑም በደለኞች ናቸው።

      መሠዊያዎቻቸውን የሚሰባብር፣ ዓምዶቻቸውንም የሚያፈራርስ አለ።

  • ሚክያስ 1:6
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    •  6 ሰማርያን በሜዳ እንደሚገኝ የፍርስራሽ ክምር፣

      ወይን እንደሚተከልበትም ስፍራ አደርጋታለሁ፤

      ድንጋዮቿን ወደ ሸለቆ እወረውራለሁ፤*

      መሠረቶቿንም አራቁታለሁ።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ