ሉቃስ 6:22, 23 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 22 “ሰዎች፣ በሰው ልጅ ምክንያት በሚጠሏችሁ፣+ በሚያገሏችሁ፣+ በሚነቅፏችሁና ክፉ እንደሆናችሁ አድርገው ያለስማችሁ ስም በሚሰጧችሁ* ጊዜ ሁሉ ደስተኞች ናችሁ። 23 በሰማይ ታላቅ ሽልማት ስለሚጠብቃችሁ በዚያን ቀን ሐሴት አድርጉ፤ በደስታም ፈንጥዙ፤ አባቶቻቸው በነቢያት ላይ እንዲሁ ያደርጉ ነበርና።+ ያዕቆብ 1:2 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 2 ወንድሞቼ ሆይ፣ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቁጠሩት፤+ 1 ጴጥሮስ 4:14 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 14 ለክርስቶስ ስም ስትሉ ብትነቀፉ* ደስተኞች ናችሁ፤+ ምክንያቱም የክብር መንፈስ ይኸውም የአምላክ መንፈስ በእናንተ ላይ ያርፋል።
22 “ሰዎች፣ በሰው ልጅ ምክንያት በሚጠሏችሁ፣+ በሚያገሏችሁ፣+ በሚነቅፏችሁና ክፉ እንደሆናችሁ አድርገው ያለስማችሁ ስም በሚሰጧችሁ* ጊዜ ሁሉ ደስተኞች ናችሁ። 23 በሰማይ ታላቅ ሽልማት ስለሚጠብቃችሁ በዚያን ቀን ሐሴት አድርጉ፤ በደስታም ፈንጥዙ፤ አባቶቻቸው በነቢያት ላይ እንዲሁ ያደርጉ ነበርና።+