ስለ ኢየሱስ የምታውቀው ምን ያህል ነው?
አንዲት በዩናይትድ ስቴትስ የሚኖሩ የ84 ዓመት አረጋዊት ሴት እስከ ዛሬ ከኖሩት ሁሉ የሚበልጠው ታላቅ ሰው ስለተባለው የኢየሱስ ክርስቶስን የሕይወት ታሪክ የሚተርክ ባለ 448 ገጽ ሥዕላዊ መጽሐፍ ሲናገሩ “መጽሐፍ ቅዱስን በተለያዩ ጊዜያት ከዳር እስከ ዳር አንብቤያለሁ። ታላቅ ሰው የተባለው መጽሐፍ የመጽሐፍ ቅዱስ ንባቤ ይበልጥ እንዲገባኝ አስችሎኛል” ብለዋል። መጽሐፉ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ኢየሱስ ሕይወት የሚተርከው ታሪክ ሕያው ሆኖ እንዲታያቸው አስችሏቸዋል።
“ይህን መጽሐፍ ደግሜ ደጋግሜ ባነበው አይሰለቸኝም። እስካሁን ድረስ ሰባት ጊዜ ያነበብኩት ሲሆን አሁንም እያነበብኩት ነው። አስደናቂ የሆኑት የኢየሱስ ባሕርያት ልቤን ይነኩታል። ኢየሱስ በምድር ላይ ስላሳለፈው የመጨረሻ ሳምንት ሳነብ በተለይ በመጨረሻዎቹ ሰዓቶች የደረሰበት ሥቃይና በመከራ እንጨት ላይ የተገደለበት ሁኔታ በጣም ያሳዝነኛል። ቢሆንም የሰማዩን አባታችንን ይሖዋን አክብሮታል።”
እስከ ዛሬ ከኖሩት ሁሉ የሚበልጠው ታላቅ ሰው በተባለው መጽሐፍ ውስጥ በአራቱ ወንጌሎች ውስጥ በተገለጸው የኢየሱስ ምድራዊ ሕይወት ያጋጠመውን እያንዳንዱን ሁኔታ ለማቅረብ ጥረት ተደርጓል። ስለ ኢየሱስ ተጨማሪ እውቀት እንዲያገኙ ያስችልዎታል። የዚህን መጽሐፍ አንድ ቅጂ ማግኘት ወይም መጽሐፍ ቅዱስን ያለ ክፍያ ማጥናት የሚፈልጉ ከሆነ የይሖዋ ምሥክሮች፣ ፖ. ሣ. ቁ. 5522፣ አዲስ አበባ ብለው ወይም በገጽ 5 ላይ ካሉት አድራሻዎች አመቺ ወደ ሆነው ይጻፉ።