የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • gf ትምህርት 8 ገጽ 14
  • የአምላክ ጠላቶች እነማን ናቸው?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአምላክ ጠላቶች እነማን ናቸው?
  • የአምላክ ወዳጅ መሆን ትችላለህ!
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ንቁ ሆናችሁ ኑሩ—ሰይጣን ሊውጣችሁ ይፈልጋል!
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
  • ጠላታችሁን እወቁ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018
  • ሰይጣን
    ንቁ!—2013
  • ዲያብሎስ ማን ነው?
    አምላክ ከእኛ የሚፈልገው ምንድን ነው?
ለተጨማሪ መረጃ
የአምላክ ወዳጅ መሆን ትችላለህ!
gf ትምህርት 8 ገጽ 14

ትምህርት 8

የአምላክ ጠላቶች እነማን ናቸው?

የአምላክ ቀንደኛ ጠላት ሰይጣን ዲያብሎስ ነው። ሰይጣን በይሖዋ ላይ ያመፀ መንፈሳዊ ፍጡር ነው። ሰይጣን ከአምላክ ጋር መዋጋቱንና በሰዎች ላይ ከፍተኛ መከራ ማድረሱን ቀጥሎበታል። ሰይጣን ክፉ ነው። እርሱ ውሸታምና ነፍሰ ገዳይ ነው።—ዮሐንስ 8:44

አጋንንት

ሌሎች መንፈሳዊ ፍጡራን ከሰይጣን ጋር አብረው በአምላክ ላይ ዓመፁ። መጽሐፍ ቅዱስ እነዚህን ፍጥረታት አጋንንት በማለት ይጠራቸዋል። እንደ ሰይጣን ሁሉ አጋንንትም የሰው ልጆች ጠላት ናቸው። ሰዎችን መጉዳት ደስ ይላቸዋል። (ማቴዎስ 9:32, 33፤ 12:22) ይሖዋ ሰይጣንንና አጋንንቱን ለዘላለም ያጠፋቸዋል። በሰዎች ላይ ችግር መፍጠራቸውን የሚቀጥሉት ለአጭር ጊዜ ብቻ ነው።—ራእይ 12:12

የአምላክ ወዳጅ ለመሆን ከፈለግህ ሰይጣን እንድታደርግ የሚፈልጋቸውን ነገሮች ማድረግ የለብህም። ሰይጣንና አጋንንቱ ይሖዋን አይወዱትም። እነሱ የአምላክ ጠላቶች ናቸው፤ አንተም የአምላክ ጠላት እንድትሆን ይፈልጋሉ። ከሰይጣን ወይም ከይሖዋ ማንን ማስደሰት እንደምትፈልግ መምረጥ ይኖርብሃል። የዘላለም ሕይወት የምትፈልግ ከሆነ የአምላክን ፈቃድ ለማድረግ መምረጥ አለብህ። ሰይጣን ሰዎችን የሚያታልልበት በርካታ ዘዴዎችና መንገዶች አሉት። ብዙ ሰዎች በእርሱ እየተታለሉ ነው።—ራእይ 12:9

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ