የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • scl ገጽ 27-29
  • ማበረታቻ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ማበረታቻ
  • ጥቅሶች ለክርስቲያናዊ ሕይወት
ጥቅሶች ለክርስቲያናዊ ሕይወት
scl ገጽ 27-29

ማበረታቻ

የአምላክ አገልጋዮች እርስ በርስ መበረታታታቸው አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?

ኢሳ 35:3, 4፤ ቆላ 3:16፤ 1ተሰ 5:11፤ ዕብ 3:13

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • 2ዜና 32:2-8—ንጉሥ ሕዝቅያስ ኃይለኛ ጠላት ሲመጣባቸው ሕዝቡን አበረታቷል

    • ዳን 10:2, 8-11, 18, 19—አረጋዊው ነቢይ ዳንኤል ኃይሉ በተሟጠጠበት ወቅት አንድ መልአክ አበረታቶታል እንዲሁም አጠናክሮታል

ኃላፊነት ያላቸው ወንድሞች ማበረታቻ ከመስጠት ጋር በተያያዘ ምን ግዴታ አለባቸው?

ኢሳ 32:1, 2፤ 1ጴጥ 5:1-3

በተጨማሪም ማቴ 11:28-30⁠ን ተመልከት

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዘዳ 3:28፤ 31:7, 8—ነቢዩ ሙሴ፣ ይሖዋ በሰጠው መመሪያ መሠረት ተተኪውን ኢያሱን አበረታቶታል እንዲሁም አደፋፍሮታል

    • ሥራ 11:22-26፤ 14:22—ሐዋርያቱ ጳውሎስና በርናባስ በስደት ወቅት የአንጾኪያ ክርስቲያኖችን አበረታተዋል

ማበረታቻ ለመስጠት ከልብ ማመስገን አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?

ምሳሌ 31:28, 29፤ 1ቆሮ 11:2

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • መሳ 11:37-40—የእስራኤል ሴቶች የመስፍኑን ዮፍታሔ ልጅ በየዓመቱ እየሄዱ ይጠይቋታል፤ ሕይወቷን ለይሖዋ አገልግሎት በመስጠቷ ያመሰግኗታል

    • ራእይ 2:1-4—ኢየሱስ የኤፌሶን ክርስቲያኖችን ማረም ቢያስፈልገውም መልካም ጎናቸውን ጠቅሶላቸዋል

ታማኝ የይሖዋ አገልጋዮች እርስ በርስ መበረታታት የሚችሉት እንዴት ነው?

ምሳሌ 15:23፤ ኤፌ 4:29፤ ፊልጵ 1:13, 14፤ ቆላ 4:6፤ 1ተሰ 5:14

በተጨማሪም 2ቆሮ 7:13, 15, 16⁠ን ተመልከት

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • 1ሳሙ 23:16-18—ዮናታን አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያለውን ዳዊትን ፈልጎ አገኘው፤ እንዲሁም በዕድሜ የሚያንሰውን ወዳጁን አበረታታው

    • ዮሐ 16:33—ኢየሱስ ምሳሌ በመሆን ተከታዮቹን አበረታቷቸዋል፤ የእሱን ምሳሌ ከተከተሉ አሸናፊዎች እንደሚሆኑ አረጋግጦላቸዋል

    • ሥራ 28:14-16—ሐዋርያው ጳውሎስ ይግባኙ እንዲታይለት ወደ ሮም በተጓዘበት ወቅት እሱን ለማግኘትና ለማበረታታት ሩቅ መንገድ ተጉዘው የመጡ ታማኝ ወንድሞቹን ሲያይ ተበረታታ

አክብሮት የማጣት ወይም የማጉረምረም መንፈስ እንዳያድርብን መጠንቀቅ ያለብን ለምንድን ነው?

ፊልጵ 2:14-16፤ ይሁዳ 16-19

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዘኁ 11:10-15—ነቢዩ ሙሴ፣ አሉታዊና ዓመፀኛ በሆነው ሕዝብ የተነሳ ተስፋ ቆርጧል

    • ዘኁ 13:31, 32፤ 14:2-6—አሥሩ ሰላዮች የነዙት መጥፎ ወሬ ሕዝቡን ተስፋ አስቆረጠ፤ ወደ ዓመፅም መራቸው

ከእምነት ባልንጀሮቻችን ጋር ጊዜ ማሳለፍ የሚያበረታታን ለምንድን ነው?

ምሳሌ 27:17፤ ሮም 1:11, 12፤ ዕብ 10:24, 25፤ 12:12

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • 2ዜና 20:1-19—ንጉሥ ኢዮሳፍጥ ታላቅ ሠራዊት ሲመጣበት አንድ ላይ ሆኖ ለመጸለይ ሕዝቡን ሰብስቧል

    • ሥራ 12:1-5, 12-17—ሐዋርያው ያዕቆብ በተገደለበትና ሐዋርያው ጴጥሮስ በታሰረበት ወቅት በኢየሩሳሌም ያለው ጉባኤ አንድ ላይ ተሰብስቦ ጸልዮአል

አዎንታዊ አመለካከት አስቸጋሪ ጊዜን በጽናት ለማለፍ ብርታት የሚሰጠን እንዴት ነው?

ሥራ 5:40, 41፤ ሮም 8:35-39፤ 1ቆሮ 4:11-13፤ 2ቆሮ 4:16-18፤ 1ጴጥ 1:6, 7

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዘፍ 39:19-23፤ 40:1-8—ዮሴፍ በሐሰት ተወንጅሎ በግፍ እስር ቤት ተጥሏል፤ ያም ሆኖ ታማኝነቱን ጠብቋል፤ ሌሎችን መርዳትም ያስደስተው ነበር

    • 2ነገ 6:15-17—ነቢዩ ኤልያስ ታላቅ ሠራዊት ሲመጣበት አልፈራም፤ አገልጋዩም የእሱ ዓይነት አመለካከት እንዲኖረው ጸልዮአል

ከይሖዋ ቃል ማበረታቻ ማግኘት

ይሖዋ ምን ማረጋገጫ ሰጥቶናል?

መዝ 55:22፤ 94:14፤ ሮም 8:38, 39፤ 1ቆሮ 10:13

በይሖዋ ትዕግሥትና ምሕረት ላይ ማሰላሰላችን የሚያበረታታን እንዴት ነው?

ነህ 9:17፤ መዝ 103:13, 14፤ 2ጴጥ 3:9, 15

ይሖዋ ጉልበታቸው እንደተሟጠጠ ለሚሰማቸው ሰዎች ምን ሊያደርግላቸው ይችላል?

መዝ 46:1፤ ኢሳ 12:2፤ 40:29-31፤ ፊልጵ 4:13

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • 1ሳሙ 1:10, 11, 17, 18—ይሖዋ በጭንቀትና በምሬት የተዋጠችው ሐና ወደ እሱ ስትጸልይ ሰምቷታል፤ ሥቃይዋ ቀለል እንዲልላትም አድርጓል

    • 1ነገ 19:1-19—ነቢዩ ኤልያስ ተስፋ በቆረጠበት ወቅት ይሖዋ ተግባራዊ እርዳታ ሰጥቶታል። ስለ ወደፊቱ ጊዜ ተስፋ በመስጠት አበረታቶታል እንዲሁም አጽናንቶታል

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ወደፊቱ ጊዜ የሚሰጠው ተስፋ የሚያበረታታን እንዴት ነው?

2ዜና 15:7፤ መዝ 27:13, 14፤ ዕብ 6:17-19፤ 12:2

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ኢዮብ 14:1, 2, 7-9, 13-15—ኢዮብ ስሜቱ እጅግ በተደቆሰበት ወቅትም እንኳ በትንሣኤ ተስፋ ተጽናንቷል

    • ዳን 12:13—ነቢዩ ዳንኤል 100 ዓመት ገደማ ሳለ አንድ መልአክ ስለ ወደፊት ሽልማቱ በመንገር አበረታቶታል

ወደ ይሖዋ መጸለይና ስለ እሱ ማሰላሰል የሚያበረታታን ለምንድን ነው?

መዝ 18:6፤ 56:4, 11፤ ዕብ 13:6

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • 1ሳሙ 30:1-9—ንጉሥ ዳዊት ከባድ ችግር በገጠመው ወቅት ወደ ይሖዋ ዘወር በማለት ብርታት አግኝቷል

    • ሉቃስ 22:39-43—ኢየሱስ በምድራዊ ሕይወቱ እጅግ ተፈታታኝ በሆነ ወቅት ላይ አጥብቆ ጸልዮአል፤ ይሖዋም የሚያበረታታው መልአክ በመላክ መልስ ሰጥቶታል

ጥሩ ዜና መስማትና ለሌሎች ማጋራት የሚያበረታታን እንዴት ነው?

ምሳሌ 15:30፤ 25:25፤ ኢሳ 52:7

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ሥራ 15:2-4—ሐዋርያቱ ጳውሎስና በርናባስ የጎበኟቸውን ጉባኤዎች በእጅጉ አበረታተዋል

    • 3ዮሐ 1-4—አረጋዊው ሐዋርያው ዮሐንስ፣ እውነትን ያስተማራቸው ሰዎች በታማኝነት እየተመላለሱ እንዳሉ መስማቱ በጣም አበረታቶታል

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ