የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • scl ገጽ 32-34
  • ምሕረት

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ምሕረት
  • ጥቅሶች ለክርስቲያናዊ ሕይወት
ጥቅሶች ለክርስቲያናዊ ሕይወት
scl ገጽ 32-34

ምሕረት

ምሕረት ምን ያካትታል?

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • መዝ 51:1, 2—ንጉሥ ዳዊት፣ ይሖዋን ምሕረት ሲለምን ይቅር እንዲለውና ከኃጢአቱ እንዲያነጻው መጠየቁ ነው

    • ሉቃስ 10:29-37—ኢየሱስ ለአንድ አይሁዳዊ ደግነትና አሳቢነት ስላሳየ ሳምራዊ ምሳሌ በመናገር ስለ ምሕረት አስተምሯል

ሁሉም የሰው ልጆች ምሕረት የሚያስፈልጋቸው ለምንድን ነው?

መዝ 130:3፤ መክ 7:20፤ 1ዮሐ 1:8

በተጨማሪም 1ነገ 8:46-50⁠ን ተመልከት

ምሕረት በማሳየት ረገድ ይሖዋ ምን ምሳሌ ትቷል?

ዘፀ 34:6፤ ነህ 9:17፤ መዝ 103:8፤ 2ቆሮ 1:3

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ኢዮብ 42:1, 2, 6-10፤ ያዕ 5:11—ይሖዋ ለኢዮብ ምሕረት በማሳየት እሱም በበኩሉ መሐሪ እንዲሆን አስተምሮታል

    • ሉቃስ 15:11-32—ኢየሱስ፣ አንድ አባት ንስሐ ገብቶ ወደ ቤቱ የተመለሰ ዓመፀኛ ልጁን እንዴት እንደተቀበለው የሚያሳይ ምሳሌ በመናገር ስለ ይሖዋ ምሕረት አስተምሯል

ይሖዋ ምሕረት የሚያደርግልን ለምንድን ነው?

ሮም 5:8፤ 1ዮሐ 4:9, 10

በተጨማሪም ቲቶ 3:4, 5⁠ን ተመልከት

የኃጢአት ይቅርታ እንድናገኝ የክርስቶስ መሥዋዕት ምን ሚና አለው?

ሉቃስ 24:47፤ ሥራ 10:43፤ 1ዮሐ 1:7, 9

ምሕረት መለመን ያለብን እንዲሁም ይህን ስጦታ አቅልለን ልንመለከተው የማይገባው ለምንድን ነው?

ሉቃስ 11:2-4፤ ዕብ 4:16

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • መዝ 51:1-4—በኃጢአቱ የተነሳ በበደለኝነት ስሜት የተደቆሰው ንጉሥ ዳዊት፣ ይሖዋ ምሕረት እንዲያደርግለት በትሕትና ለምኗል

    • ሉቃስ 18:9-14—ኢየሱስ፣ ይሖዋ ምሕረት የሚያሳየው ድክመታቸውን በትሕትና አምነው ለሚቀበሉ ሰዎች እንደሆነ በምሳሌ አስረድቷል

ከባድ ኃጢአት የሠሩ ሰዎችም እንኳ ይሖዋ ምሕረት እንደሚያደርግላቸው ተስፋ ማድረግ የሚችሉት ለምንድን ነው?

ዘዳ 4:29-31፤ ኢሳ 55:7

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • 2ዜና 33:9-13, 15—እጅግ ክፉ የነበረው ንጉሥ ምናሴ ንስሐ ገብቶ ምሕረት ለመነ፤ ወደ ንግሥናው ከተመለሰ በኋላም በእርግጥ ለውጥ ማድረጉን በተግባር አሳይቷል

    • ዮናስ 3:4-10—ጨካኝና ደም አፍሳሽ የነበሩት የነነዌ ሰዎች ንስሐ በመግባታቸው የአምላክን ምሕረት አግኝተዋል

አንድ ኃጢአተኛ መናዘዙና አካሄዱን መቀየሩ የይሖዋን ምሕረት ለማግኘት የሚረዳው እንዴት ነው?

መዝ 32:5፤ ምሳሌ 28:13፤ 1ዮሐ 1:9

ይሖዋ ምሕረት ስላደረገልን ብቻ ከቅጣት ወይም ኃጢአታችን ከሚያስከትልብን መዘዝ እናመልጣለን ማለት አይደለም

ዘፀ 34:6, 7፤ 2ሳሙ 12:9-13

መሐሪ መሆን ያለብን ለምንድን ነው?

ማቴ 6:14፤ ሉቃስ 6:36፤ ቆላ 3:13

ለሌሎች ምሕረት አለማሳየታችን ከይሖዋ ጋር ያለንን ዝምድና የሚነካው እንዴት ነው?

ማቴ 9:13፤ 23:23፤ ያዕ 2:13

በተጨማሪም ምሳሌ 21:13⁠ን ተመልከት

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ማቴ 18:23-35—ኢየሱስ፣ ምሕረት የማያደርግ ሰው የይሖዋን ምሕረት እንደማያገኝ በምሳሌ አስረድቷል

    • ሉቃስ 10:29-37—በሰፊው የሚታወቅ አንድ የኢየሱስ ምሳሌ እንደሚጠቁመው ይሖዋና ኢየሱስ ምሕረት በማያደርጉ ሰዎች አይደሰቱም፤ እንደ መሐሪው ሳምራዊ ባሉ ሰዎች ግን ይደሰታሉ

ይሖዋ መሐሪ ለሆኑ ሰዎች ምን ያደርግላቸዋል?

ማቴ 5:7፤ ማር 11:25

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ