የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • scl ገጽ 108-109
  • ጥናት

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ጥናት
  • ጥቅሶች ለክርስቲያናዊ ሕይወት
ጥቅሶች ለክርስቲያናዊ ሕይወት
scl ገጽ 108-109

ጥናት

አንድ ክርስቲያን የአምላክን ቃል አዘውትሮ ማጥናት ያለበት ለምንድን ነው?

መዝ 1:1-3፤ ምሳሌ 18:15፤ 1ጢሞ 4:6፤ 2ጢሞ 2:15

በተጨማሪም ሥራ 17:11⁠ን ተመልከት

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • መዝ 119:97-101—መዝሙራዊው ለአምላክ ሕግ ስላለው ፍቅር እንዲሁም ሕጉን በሕይወቱ ውስጥ ተግባራዊ ማድረጉ ስላስገኘለት ጥቅሞች በመንፈስ መሪነት ጽፏል

    • ዳን 9:1-3 ግርጌ—ዳንኤል ቅዱሳን መጻሕፍትን በማጥናት፣ እስራኤላውያን በግዞት የሚቆዩባቸው 70 ዓመታት ማብቂያ እንደተቃረበ ተረዳ

እውቀት መቅሰማችንን መቀጠል ያለብን ለምንድን ነው?

ዕብ 6:1-3፤ 2ጴጥ 3:18

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ምሳሌ 4:18—የማለዳ ብርሃን እየደመቀ እንደሚሄድ ሁሉ መንፈሳዊ ሰው ስለ መጽሐፍ ቅዱስ እውነት ያለው ግንዛቤም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠራ ይሄዳል፤ ምክንያቱም ይሖዋ የመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችን የሚገልጠው ደረጃ በደረጃ ነው

    • ማቴ 24:45-47—ኢየሱስ በመጨረሻዎቹ ቀናት መንፈሳዊ ምግብ በወቅቱ የሚያቀርብ “ታማኝና ልባም ባሪያ” እንደሚሾም አስቀድሞ ተናግሯል

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥበብ ሰብዓዊ ፍልስፍናን በያዙ መጻሕፍት ላይ ካለው ከማንኛውም ጥበብ የላቀው ለምንድን ነው?

መክ 12:11-13፤ 1ቆሮ 3:19፤ 1ጢሞ 6:20, 21፤ 2ጴጥ 1:19-21

ይሖዋ መጽሐፍ ቅዱስን በቅንነት ለሚያጠኑ ሰዎች ምን እንደሚሰጣቸው ቃል ገብቷል?

ምሳሌ 2:4-6፤ 9:10፤ ዮሐ 6:45

ከግል የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናታችን ጥቅም ለማግኘት ይሖዋ ምን እንዲሰጠን መጸለይ ያስፈልገናል?

ሉቃስ 11:13፤ 1ቆሮ 2:10፤ ያዕ 1:5

በተጨማሪም መዝ 119:66⁠ን ተመልከት

“ታማኝና ልባም ባሪያ” የሚያቀርብልንን መንፈሳዊ ምግብ በሙሉ ጥሩ አድርገን ልንጠቀምበት የሚገባው ለምንድን ነው?

ማቴ 24:45-47

በተጨማሪም ማቴ 4:4፤ 1ጢሞ 4:15⁠ን ተመልከት

ለዝርዝር ጉዳዮች ሳይቀር ትኩረት በመስጠት ትክክለኛ እውቀት ለማግኘት ጥረት ማድረግ ያለብን ለምንድን ነው?

ፊልጵ 1:9, 10፤ ቆላ 1:9, 10

ጥበብና ማስተዋል ማግኘታችን ምን ያህል አስፈላጊ ነው?

ምሳሌ 4:7፤ መክ 7:25

ረጋ ብለን እንዲሁም ቃላቱን በደንብ እያሰብን ማንበብ ያለብን ለምንድን ነው?

ኢያሱ 1:8፤ መዝ 1:2

የአምላክን ቃል በሕይወታችን ውስጥ እንዴት ተግባራዊ እንደምናደርገው ማሰብ ያለብን ለምንድን ነው?

ሮም 15:4፤ 1ቆሮ 10:11፤ 2ጢሞ 3:16, 17፤ ያዕ 1:22-25

የተማርነውን ነገር ለሌሎች እንዴት እንደምናካፍል ማሰላሰል ያለብን ለምንድን ነው?

ምሳሌ 15:28፤ 1ጴጥ 3:15

አስፈላጊ እውነቶችን ደጋግመን ማጥናታችን ምን ጥቅም አለው?

2ጴጥ 1:13፤ 3:1, 2

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዘዳ 6:6, 7፤ 11:18-20—ይሖዋ፣ ሕዝቡ የእሱን ቃል በልጆቻቸው ልብ ውስጥ እንዲቀርጹና ደጋግመው እንዲያስተምሯቸው አዟቸዋል

የአምላክን ቃል በቤተሰብ መወያየት ምን ጥቅም አለው?

ኤፌ 6:4

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዘፍ 18:17-19—አብርሃም ጽድቅ ስለሆነው የሕይወት መንገድ ቤተሰቡን እንዲያስተምር ይሖዋ ነግሮታል

    • መዝ 78:5-7—በእስራኤል ብሔር ውስጥ እያንዳንዱ ትውልድ ቀጣዩን ትውልድ እንዲያስተምር ይጠበቅበት ነበር፤ የዚህም ዓላማ ሕዝቡ በትውልዶቹ ሁሉ በይሖዋ ታምኖ እንዲኖር ነው

ከጉባኤው ጋር አብረን ማጥናት የሚጠቅመን እንዴት ነው?

ዕብ 10:25

በተጨማሪም ምሳሌ 18:1⁠ን ተመልከት

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ