የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w01 9/1 ገጽ 31
  • የአንባብያን ጥያቄዎች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአንባብያን ጥያቄዎች
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2001
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • በእርግጥ ኢየሱስ የአምላክ ልጅ ነው?
    ንቁ!—2006
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2013
  • ኢየሱስ የአምላክ ልጅ ተብሎ የተጠራው ለምንድን ነው?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • የአንባቢያን ጥያቄዎች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2006
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2001
w01 9/1 ገጽ 31

የአንባብያን ጥያቄዎች

ቆላስይስ 1:​16 ስለ አምላክ ልጅ ሲናገር “ሁሉ በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል” ይላል። ‘ሁሉ ለእርሱ’ ማለትም የአምላክ ልጅ ለሆነው ለኢየሱስ ተፈጥሮአል ሲባል ምን ማለት ነው?

ይሖዋ ከራሱ ከኢየሱስ በስተቀር ሌሎች ነገሮችን ሁሉ ለመፍጠር አንድያ ልጁን ዋና ሠራተኛ አድርጎ ተጠቅሞበታል። (ምሳሌ 8:​27-30፤ ዮሐንስ 1:​3) ልጁም ከእነዚህ የፍጥረት ሥራዎች ደስታ የሚያገኝ ሲሆን ከዚህ አንጻር ሲታይ “ለእርሱ” ተፈጥረዋል መባሉ የተገባ ነው።

ሰብዓዊ ወላጆች ወንዶች ወይም ሴቶች ልጆች ሲያገኙ ደስ እንደሚላቸው እናውቃለን። በመሆኑም አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሳሌ ‘አባት ደስ ስለሚሰኝበት ልጅ’ ይናገራል። (ምሳሌ 3:​12፤ 29:​17) በተመሳሳይም ይሖዋ አምላክ ሕዝቦቹ እስራኤላውያን ታማኝ በነበሩበት ጊዜ ተደስቶባቸዋል። (መዝሙር 44:​3፤ 119:​108፤ 147:​11) አሁን እኛ እስካለንበት ዘመን ድረስ ያሉ የታመኑ ሰዎች በሚያደርጉትም ነገር ይደሰታል።​—⁠ምሳሌ 12:​22፤ ዕብራውያን 10:​38

ስለሆነም አምላክ የሥራ ባልደረባው ኢየሱስ በሥራው ውጤት እንዲደሰት ማድረጉ የተገባ ነው። እንዲያውም ምሳሌ 8:​31 ‘ከምድሩ ደስታን እንዲሁም ከሰው ልጆች ተድላን’ ያገኝ እንደነበር ይናገራል። ቆላስይስ 1:​16 “ሁሉ በእርሱና ለእርሱ ተፈጥረዋል” የሚለው ከዚህ አንጻር ነው።​—⁠በሰያፍ የጻፍነው እኛነን።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ