የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w02 6/15 ገጽ 31
  • ምሥጢርን ለመግለጥ ጊዜ አለው

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ምሥጢርን ለመግለጥ ጊዜ አለው
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
w02 6/15 ገጽ 31

ምሥጢርን ለመግለጥ ጊዜ አለው

አንዳንድ ጉዳዮችን በምሥጢር መያዝና አለመያዝ ሰላምን በማስፈን ረገድ ትልቅ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል። ይሁን እንጂ ምሥጢር የሆነውን ጉዳይ የምንገልጥበት ጊዜ ይኖራል? ነቢዩ አሞጽ ይሖዋን በሚመለከት ምን ብሎ እንደተናገረ ልብ በል:- “በእውነት ጌታ እግዚአብሔር ምሥጢሩን ለባሪያዎቹ ለነቢያት ካልነገረ በቀር ምንም አያደርግም።” (አሞጽ 3:7) ምሥጢር መጠበቅን በተመለከተ ከእነዚህ ቃላት አንድ ነገር ልንማር እንችላለን። ይሖዋ ለተወሰነ ጊዜ አንዳንድ ጉዳዮችን በምሥጢር ሊይዝና ከጊዜ በኋላ ለአንዳንድ ግለሰቦች ሊያሳውቃቸው ይችላል። በዚህ ረገድ ይሖዋን ልንመስለው የምንችለው እንዴት ነው?

አንዳንድ ጊዜ በክርስቲያን ጉባኤ ውስጥ ያሉ የተሾሙ እረኞች አንድን ጉዳይ በምሥጢር መያዙን አስፈላጊ ሆኖ ሊያገኙት ይችላሉ። (ሥራ 20:28) ለምሳሌ ያህል ለጉባኤው ጥቅም በማሰብ አንዳንድ ዝግጅቶችን ወይም በጉባኤ ኃላፊነት ረገድ የተደረጉ ለውጦችን ዝርዝር እስከ ተወሰነ ጊዜ ድረስ በምሥጢር ለመያዝ ይወስኑ ይሆናል።

ይሁን እንጂ በዚህ ጊዜ ምሥጢሩ መቼና እንዴት ባለ ሁኔታ ይፋ እንደሚሆን ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ሰዎች ግልጽ ማድረጉ አስፈላጊ ነው። አንድ ጉዳይ ይፋ የሚደረገው መቼ እንደሆነ ማወቃቸው ያ ጊዜ እስኪደርስ ድረስ በምሥጢር እንዲይዙት ሊረዳቸው ይችላል።​​—⁠⁠ምሳሌ 25:9

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ