የግንባታ ፕሮጀክት ዜና
የቅርንጫፍ ቢሮው የግንባታ ሥራ እየተፋጠነ ነው! ወደ ጎን ከሰማንያ ሜትር በላይ ርዝመት ያለው ባለ ሦስት ፎቅ ሕንፃ ዋናው ሥራ የተጠናቀቀ ሲሆን ክረምት ከመግባቱ በፊት ጣሪያ እንደሚለብስ ይጠበቃል። በግንቦት ወር መጀመሪያ ላይ አብዛኞቹ ክፍሎች ተለስነዋል። ከሕንፃው በስተ ጀርባ ባለው ቦታ ላይ 1, 700 ሰዎች የመያዝ አቅም ያለው ትልቅ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የመሠረት ሥራ ተጠናቅቋል። የጥምቀት ገንዳውን፣ የልብስ መቀየሪያ ክፍሎቹን፣ ቢሮዎቹንና የሽማግሌዎች መሰብሰቢያ ክፍሉን ጨምሮ አብዛኛው የመድረኩ ሥራ ተገባዷል። በመንገዱና በመኪና ማቆሚያ ቦታዎቹ ላይ አንዳንድ የግንባታ ሥራዎች እየተካሄዱ ነው። በተጨማሪም የጀነሬተር ክፍልና ለመሰብሰቢያ አዳራሹ የመጸዳጃ ክፍሎች የሚያገለግል የፍሳሽ ማጠራቀሚያ እየተገነባ ነው። አጠቃላይ የግንባታው ሥራ ከግማሽ በላይ የተከናወነ ሲሆን በወጣለት መርሃ ግብር መሠረት በ2004 መጀመሪያ ላይ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። ለምታደርጉት የገንዘብ መዋጮ ከልብ እያመሰገንን ይሖዋ ሥራውን እንዲባርከው እንጸልያለን።