ማስታወቂያዎች
◼ የሚበረከቱ ጽሑፎች ግንቦት:- መጽሔቶች። በተመላልሶ መጠየቅ ወቅት ትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው? የተባለውን መጽሐፍ አበርክቱ። ሰኔ:- ለቤተሰብ ደስታ ቁልፉ ምንድን ነው? ሐምሌና ነሐሴ:- ብሮሹሮች።
◼ ለዓለም አቀፉ ሥራ የገንዘብ መዋጮ ለማድረግ በአውራጃ ስብሰባዎች ላይ ቼክ የሚከቱ ወይም ቼኮችን ወደ ቅርንጫፍ ቢሮ የሚልኩ ሁሉ ገንዘቡ “ለይሖዋ ምሥክሮች” (Yeyihowa Misikiroch) የሚከፈል መሆኑን ማመልከት ይኖርባቸዋል።
◼ በቅርብ ጊዜ በድጋሚ በታተመው የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ በተባለው መጽሐፍ የመጨረሻ ገጾች ላይ ለጥናት የሚረዱ ጥያቄዎች ወጥተዋል። ይህ ዝግጅት ለማስተማሩ ሥራ ጠቃሚ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ምንም ጥርጥር የለውም።
◼ የሽማግሌዎች አካላት አደጋ ከመከሰቱ በፊት ሊደረግ ስለሚገባው ቅድመ ዝግጅት የሚናገረውን የሐምሌ 6, 2006 ደብዳቤ እንደገና በማንበብ የእያንዳንዱ አስፋፊ ወቅታዊ መረጃ ያላቸው መሆኑን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል። ለአደጋ በተጋለጡ አካባቢዎች ያሉ ጉባኤዎች ድንገተኛ ሁኔታ ሲያጋጥም ወንድሞችን ቶሎ ለማግኘት የሚረዱ ተጨማሪ መረጃዎችን ማሰባሰብ አለባቸው። እርግጥ አስፋፊዎች አደጋ በሚከሰትበት ጊዜ ብቻ ሳይሆን ለእረፍት፣ ለሥራ፣ ለሕክምናና ለመሳሰሉት ጉዳዮች ረዘም ላሉ ጊዜያት ከአካባቢያቸው ርቀው ሲሄዱ ሁኔታውን ለመጽሐፍ ጥናት የበላይ ተመልካቻቸው ወይም ለሌላ ሽማግሌ ማሳወቃቸው ጠቃሚ ነው።
◼ አዲስ የደረሱን ጽሑፎች:- እንግሊዝኛ:- የ2007 የዓመት መጽሐፍ፣ ለይሖዋ የውዳሴ መዝሙር ዘምሩ በኤም ፒ 3፤ ትግርኛ:- የይሖዋን ፈቃድ ለማድረግ የተደራጀ ሕዝብ፣ ዘ ሮድ ቱ ኤቨርላስቲንግ ላይፍ—ሃቭ ዩ ፋውንድ ኢት?፤ ወላይትኛ:- አምላክ ስለ እኛ በእርግጥ ያስባል?፣ የምትወዱት ሰው ሲሞት።
◼ በድጋሚ የደረሱን ጽሑፎች:- አማርኛ:- ማመራመር፣ ነቅተህ ጠብቅ!፤ ቀለል ባለ ቻይንኛ:- የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት፣ ለሰው ሁሉ የሚሆን መጽሐፍ፣ T-19 (ይህ ዓለም ከጥፋት ይተርፍ ይሆን?)፤ ቻይንኛ:- T-14 (የይሖዋ ምሥክሮች ምን ብለው ያምናሉ?)፤ እንግሊዝኛ:- ክርኤሽን፣ ክርኤተር፣ የዳንኤል ትንቢት፣ ራእይ፣ ባለማጣቀሻው የአዲስ ዓለም ትርጉም (Rbi8)፣ ለሰው ሁሉ የሚሆን መጽሐፍ፣ ኤ ሳቲስፋይንግ ላይፍ፣ ለሰዎች ሁሉ የሚሆን ምሥራች፣ ጋይዳንስ ኦቭ ጎድ፣ የይሖዋ ምሥክሮች—እነማን ናቸው . . . ?፣ ዘ ሮድ ቱ ኤቨርላስቲንግ ላይፍ፣ T-27 (መከራና ሥቃይ ሁሉ በቅርቡ ይወገዳል!)፣ በሲዲ የተዘጋጁ የመንግሥቱ ጣዕመ ዜማዎች ቁጥር 1, 2, 3, 6, 7, 8፣ ለይሖዋ የውዳሴ መዝሙር ዘምሩ በሲዲ፣ የወጣቶች ጥያቄ—ሕይወቴን እንዴት ብጠቀምበት ይሻላል? በዲቪዲ።