የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • g00 9/8 ገጽ 18
  • “አቻ የማይገኝለት መጽሔት”

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • “አቻ የማይገኝለት መጽሔት”
  • ንቁ!—2000
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ዘመናዊ ሰማዕታት በስዊድን ምሥክርነት እየሰጡ ነው
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
  • ሕልም ሆኖ የቀረው ወረቀት አልባ ቢሮ
    ንቁ!—1999
  • ጽኑ አቋማቸውን በድፍረት የጠበቁ ምሥክሮች የናዚን ስደት በድል ተወጡ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2001
  • የሰዎችን ትኩረት የሚስቡ የተወሰኑ ርዕሶችን ምረጡ
    የመንግሥት አገልግሎታችን—1998
ለተጨማሪ መረጃ
ንቁ!—2000
g00 9/8 ገጽ 18

“አቻ የማይገኝለት መጽሔት”

የንቁ! መጽሔት አዘጋጆች በቅርቡ በዩናይትድ ስቴትስ የምትኖር አንዲት የ18 ዓመት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ የላከችው ደብዳቤ ደርሷቸው ነበር። እንዲህ ስትል ጻፈች:-

“በኮሌጅ ከሚሰጥ ትምህርት ጋር የሚመጣጠን አንድ የታሪክ ትምህርት ኮርስ ለመውሰድ ተመዘገብኩ። ከፍተኛ ጥናት የተደረገበት የጽሑፍ ሥራ ማቅረብ ያስፈልግ ስለነበር በናዚ አገዛዝ ዘመን የይሖዋ ምሥክሮች በጀርመን ስላሳዩት የሥነ ምግባር ጥንካሬ የሚገልጽ ጽሑፍ ለማዘጋጀት መረጥኩ። ስለዚህ በሐምሌ 8, 1998 የንቁ! መጽሔት እትም ላይ በወጣው ‘የይሖዋ ምሥክሮች​—⁠በናዚ ፊት ያሳዩት ድፍረት’ በሚለው ርዕሰ ትምህርት መደምደሚያ ላይ የተጠቀሰውን ተጨማሪ መረጃ የሚገኙባቸውን ጽሑፎች ዝርዝር እንድትልኩልኝ እጠይቃችኋለሁ። ጽሑፉ ከፍተኛ ጥናት የተደረገበትና አሳማኝ በሆነ መንገድ የቀረበ በመሆኑ በጽሑፉ ላይ ከተንጸባረቀው ጠንካራ ስሜትና እውነታ ከፊሉን እንኳ ወስጄ የጽሑፍ ሥራዬን ባዘጋጅ ሥራዬን ለሚገመግሙት ከፍተኛ ምሥክርነት ይሰጣል።

“እንዲህ ያለውን አቻ የማይገኝለት መጽሔት ያለማቋረጥ የምታዘጋጁ በመሆናችሁ ላመሰግናችሁ እወዳለሁ። በእያንዳንዱ እትም ላይ በትምህርት ቤት ላገኘው ከምችለው የላቀ ‘የሥነ ጽሑፍ ትምህርት’ አገኛለሁ። ይህም በእያንዳንዱ በማዘጋጀው የሥነ ጽሑፍ ሥራዬ ማሻሻያ ለማድረግ እንድጣጣር አነሳስቶኛል። ጥረታችሁን የማደንቅ መሆኔን ልገልጽላችሁ እወዳለሁ።”

[በገጽ 18 ላይ የሚገኝ የሥዕል ምንጭ]

መሃል ላይ ያለው ፎቶ:- Państwowe Muzeum Oświęcim-Brzezinka, courtesy of the USHMM Photo Archives

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ