የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • my ታሪክ 53
  • ዮፍታሔ የገባው ቃል

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ዮፍታሔ የገባው ቃል
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • አባቷንና ይሖዋን አስደስታለች
    ልጆቻችሁን አስተምሩ
  • በአምላክም ሆነ በጓደኞቿ ዘንድ ተወዳጅ ነበረች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2011
  • ዮፍታሔ የገባው ቃል
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • በይሖዋ ላይ እምነት ማሳደር የእሱን ሞገስ ያስገኛል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2016
ለተጨማሪ መረጃ
የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
my ታሪክ 53

ምዕራፍ 53

ዮፍታሔ የገባው ቃል

ቃል ከገባህ በኋላ የገባኸውን ቃል መጠበቅ አስቸጋሪ ሆኖብህ ያውቃል? እዚህ ሥዕል ላይ የምታየው ሰው ይህ ሁኔታ አጋጥሞታል፤ በጣም ያዘነውም በዚህ ምክንያት ነው። ይህ ሰው ደፋሩ የእስራኤል መስፍን ዮፍታሔ ነው።

ዮፍታሔ ይኖር የነበረው እስራኤላውያን ይሖዋን ማምለክ ትተው በነበረበት ዘመን ነበር። እስራኤላውያን እንደገና መጥፎ ነገር እየሠሩ ነበር። ስለዚህ ይሖዋ የአሞን ሰዎች እንዲያሠቃዩአቸው ፈቀደ። ይህም እስራኤላውያን ‘በአንተ ላይ ኃጢአት ሠርተናል። እባክህ አድነን!’ ብለው ወደ ይሖዋ እንዲጮኹ አደረጋቸው።

ሕዝቡ መጥፎ ነገር በመሥራታቸው ተጸጸቱ። ይሖዋን እንደገና በማምለክ በሠሩት ሥራ መጸጸታቸውን በተግባር አሳዩ። ስለዚህ ይሖዋ እንደገና ረዳቸው።

ሕዝቡ መጥፎዎቹን አሞናውያንን እንዲወጋላቸው ዮፍታሔን መረጡት። ዮፍታሔ ይሖዋ በውጊያው እንዲረዳው በጣም ፈልጎ ነበር። ስለዚህ እንዲህ ሲል ለይሖዋ ቃል ገባ:- ‘አሞናውያንን እንዳሸንፍ ካደረግኸኝ ስመለስ እኔን ለመቀበል ከቤቴ መጀመሪያ የሚወጣውን ሰው ለአንተ እሰጠዋለሁ።’

ይሖዋ ዮፍታሔ የገባውን ቃል ሰምቶ ድል እንዲያገኝ ረዳው። ዮፍታሔ ወደ ቤቱ ሲመለስ እሱን ለመቀበል መጀመሪያ የወጣው ሰው ማን እንደሆነ ታውቃለህ? ሴት ልጁ ነች፤ ከእሷ ሌላ ልጅ የለውም። ‘ወይኔ ልጄ!’ በማለት ዮፍታሔ ጮኸ። ‘ምን ዓይነት ሐዘን ነው ያመጣሽብኝ! አንዴ ለይሖዋ ቃል ገብቻለሁ፤ የገባሁትን ቃል ማፍረስ አልችልም።’

የዮፍታሔ ልጅ የገባውን ቃል ስትሰማ በመጀመሪያ እሷም አዝና ነበር። ምክንያቱም አባቷንና ጓደኞቿን ትታ መሄዷ ነው። ይሁን እንጂ ቀሪውን ሕይወቷን በሴሎ በሚገኘው በማደሪያው ድንኳን ይሖዋን በማገልገል ታሳልፋለች። ስለዚህ አባቷን ‘ለይሖዋ ቃል ከገባህ ቃልህን መጠበቅ አለብህ’ አለችው።

የዮፍታሔ ልጅ ወደ ሴሎ ሄደችና ቀሪውን ሕይወቷን በማደሪያው ድንኳን ውስጥ ይሖዋን በማገልገል አሳለፈች። የእስራኤል ሴቶች እሷን ለመጠየቅ በየዓመቱ ለአራት ቀናት ወደዚያ ይሄዱና አንድ ላይ ሆነው አስደሳች የሆነ ጊዜ ያሳልፉ ነበር። የዮፍታሔ ልጅ ጥሩ የይሖዋ አገልጋይ ስለነበረች ሕዝቡ ይወዷት ነበር።

መሳፍንት 10:​6-18፤ 11:​1-40

የአንቀጾቹ ጥያቄዎች

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ