የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • my ታሪክ 67
  • ኢዮሣፍጥ በይሖዋ ተማመነ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ኢዮሣፍጥ በይሖዋ ተማመነ
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ይሖዋ ኢዮሳፍጥን ከጠላቶቹ አዳነው
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • አስቀድሞ ለተጻፉት ነገሮች ትኩረት ትሰጣላችሁ?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2017
  • ለሌሎች የይሖዋ ዓይነት አመለካከት ይኑራችሁ
    ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2023
  • ይሖዋን በሙሉ ልብ አገልግሉ!
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2017
ለተጨማሪ መረጃ
የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
my ታሪክ 67

ምዕራፍ 67

ኢዮሣፍጥ በይሖዋ ተማመነ

እነዚህ ሰዎች እነማን እንደሆኑና ምን እያደረጉ እንዳሉ ታውቃለህ? ወደ ጦርነት እየሄዱ ነው፤ ከፊታቸው ያሉት ሰዎች ደግሞ እየዘመሩ ነው። ይሁን እንጂ ‘እየዘመሩ ያሉት ሰዎች የሚዋጉበት ሰይፍና ጦር ያልያዙት ለምንድን ነው?’ ብለህ ትጠይቅ ይሆናል። ለምን እንደሆነ እስቲ እንመልከት።

ኢዮሣፍጥ ሁለቱን ነገዶች ያቀፈው የእስራኤል መንግሥት ንጉሥ ነው። ኢዮሣፍጥ ይኖር የነበረው አሥሩን ነገዶች የያዘውን ሰሜናዊ መንግሥት ያስተዳድሩ የነበሩት ንጉሥ አክዓብና ኤልዛቤል በኖሩበት ዘመን ነው። ይሁን እንጂ ኢዮሣፍጥ ጥሩ ንጉሥ ነበር፤ አባቱ አሳም ጥሩ ንጉሥ ነበር። ስለዚህ ሁለቱን ነገዶች ባቀፈው የደቡብ መንግሥት ሥር የነበሩት ሰዎች ለብዙ ዓመታት ጥሩ ኑሮ ይኖሩ ነበር።

ይሁን እንጂ አሁን ሕዝቡን ፍርሃት ላይ የጣለ አንድ ነገር ተከስቷል። መልእክተኞች ወደ ኢዮሣፍጥ መጥተው ‘ከሞዓብ፣ ከአሞንና ከሴይር ተራራ አገሮች የተውጣጣ አንድ ትልቅ ሠራዊት አንተን ለመውጋት እየገሰገሰ ነው’ አሉት። ብዙ እስራኤላውያን የይሖዋን እርዳታ ለመጠየቅ ወደ ኢየሩሳሌም ተሰበሰቡ። ወደ ቤተ መቅደሱ ሄዱ፤ በቤተ መቅደሱም ኢዮሣፍጥ ‘አምላካችን ይሖዋ ሆይ፣ ምን እንደምናደርግ አናውቅም። ይህን ትልቅ ሠራዊት መቋቋም አንችልም። እንድትረዳን እንማጸንሃለን’ ሲል ጸለየ።

ይሖዋ ጸሎቱን ሰማና ከአገልጋዮቹ መካከል አንዱ ሕዝቡን እንዲህ ሲል እንዲነግራቸው አደረገ:- ‘ውጊያው የእናንተ ሳይሆን የአምላክ ነው። እናንተ መዋጋት አያስፈልጋችሁም። ዝም ብላችሁ ቁሙና ይሖዋ እንዴት እንደሚያድናችሁ ተመልከቱ።’

ስለዚህ በነጋታው ጠዋት ኢዮሣፍጥ ሕዝቡን ‘በይሖዋ ተማመኑ!’ አላቸው። ከዚያም ከወታደሮቹ ፊት መዘምራኑ እንዲሄዱ አደረገ፤ በሚጓዙበት ጊዜም ለይሖዋ የውዳሴ መዝሙር ይዘምሩ ነበር። ወደ ውጊያው ቦታ እየቀረቡ ሲሄዱ ምን እንደተፈጸመ ታውቃለህ? ይሖዋ የጠላት ወታደሮች እርስ በርሳቸው እንዲፋጁ አደረጋቸው። እስራኤላውያን ወደ ቦታው ሲደርሱ የጠላት ወታደር በሙሉ ሞቶ ነበር!

ኢዮሣፍጥ በይሖዋ መታመኑ ጥበብ አልነበረምን? እኛም በይሖዋ መታመናችን ጥበብ ነው።

1 ነገሥት 22:​41-53፤ 2 ዜና መዋዕል 20:​1-30

የአንቀጾቹ ጥያቄዎች

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ