የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • my ታሪክ 96
  • ኢየሱስ የታመሙ ሰዎችን ፈወሰ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ኢየሱስ የታመሙ ሰዎችን ፈወሰ
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ኢየሱስ ንጉሥ ሆኖ መጣ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ለሥራም ሆነ ለእረፍት “ጊዜ አለው”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2019
  • ክርስቲያኖች ሰንበትን ማክበር ይኖርባቸዋል?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • ሰንበት
    ከቅዱሳን ጽሑፎች እየጠቀሱ ማመራመር
ለተጨማሪ መረጃ
የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
my ታሪክ 96

ምዕራፍ 96

ኢየሱስ የታመሙ ሰዎችን ፈወሰ

ኢየሱስ በሄደበት ሁሉ የታመሙ ሰዎችን ይፈውስ ነበር። በየመንደሩና በየከተሞቹ የሚኖሩ ሁሉ ኢየሱስ ስለፈጸማቸው ተአምራት ሰሙ። ስለዚህ ሰዎች አካለ ስንኩሎችን፣ ዓይነ ስውሮችን፣ መስማት የተሳናቸውንና ሌሎች የታመሙ ብዙ ሰዎችን ወደ ኢየሱስ አመጡአቸው። ኢየሱስ ሁሉንም ፈወሳቸው።

ዮሐንስ ኢየሱስን ካጠመቀው ከሦስት ዓመት በላይ አልፎ ነበር። ኢየሱስ ሐዋርያቱን ብዙም ሳይቆይ ወደ ኢየሩሳሌም እንደሚሄድና በዚያም እንደሚገደል፣ ከዚያም ከሞት እንደሚነሳ ነገራቸው። እስከዚያው ድረስ ግን ኢየሱስ የታመሙ ሰዎችን መፈወሱን ቀጥሎ ነበር።

ከዕለታት አንድ ቀን ኢየሱስ በሰንበት እያስተማረ ነበር። ሰንበት አይሁዳውያን የሚያርፉበት ቀን ነው። ሥዕሉ ላይ የምታያት ሴት በጣም ታማ ነበር። ለ18 ዓመታት ያህል ጎብጣ ነበር፤ ቀጥ ብላ መቆም አትችልም ነበር። ስለዚህ ኢየሱስ እጁን ጫነባትና ቀጥ ብላ ቆመች። ተፈወሰች!

ይህ የሃይማኖት መሪዎቹን አስቆጣቸው። ከእነርሱ መካከል አንዱ ሕዝቡን ‘ሥራ የምንሠራባቸው ስድስት ቀኖች አሉ። ከበሽታችሁ ለመዳን መጥታችሁ መፈወስ የምትችሉት በእነዚህ ቀኖች እንጂ በሰንበት አይደለም!’ አላቸው።

ኢየሱስ ግን እንዲህ ሲል መለሰላቸው:- ‘እናንተ ክፉዎች፣ ማናችሁም ብትሆኑ በሰንበት ቀን አህያችሁን ከታሰረበት ፈትታችሁ ውኃ ለማጠጣት ትወስዱታላችሁ። ታዲያ ለ18 ዓመታት ታማ የኖረችው ይቺ ምስኪን ሴት በሰንበት መፈወስ አይገባትም?’ የኢየሱስ መልስ እነዚህን ክፉ ሰዎች አሳፈራቸው።

በኋላ ኢየሱስና ሐዋርያቱ ወደ ኢየሩሳሌም መጓዝ ጀመሩ። ልክ ከኢያሪኮ እንደወጡ ሁለት ዓይነ ስውር ለማኞች ኢየሱስ በዚያ በኩል እያለፈ እንዳለ ሰሙ። ስለዚህ ‘ኢየሱስ ሆይ፣ እርዳን!’ እያሉ ጮኹ።

ኢየሱስ ዓይነ ስውሮቹን ጠርቶ ‘ምን እንዳደርግላችሁ ትፈልጋላችሁ?’ አላቸው። ‘ጌታ ሆይ፣ ዓይኖቻችን እንዲከፈቱ አድርግልን’ አሉት። ኢየሱስ ዓይኖቻቸውን ዳሰሳቸው፤ ወዲያውኑ ማየት ቻሉ! ኢየሱስ እነዚህን ሁሉ አስደናቂ ተአምራት ይፈጽም የነበረው ለምን እንደሆነ ታውቃለህ? ሰዎችን ይወድ ስለነበረና በእርሱ እንዲያምኑ ይፈልግ ስለነበረ ነው። እንግዲያው እኛም ንጉሥ ሆኖ በሚገዛበት ጊዜ በምድር ላይ የሚኖር ማንም ሰው ዳግመኛ እንደማይታመም እርግጠኞች መሆን እንችላለን።

ማቴዎስ 15:​30, 31፤ ሉቃስ 13:​10-17፤ ማቴዎስ 20:​29-34

የአንቀጾቹ ጥያቄዎች

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ