የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • my ታሪክ 99
  • ፎቅ ላይ በሚገኝ አንድ ክፍል ውስጥ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ፎቅ ላይ በሚገኝ አንድ ክፍል ውስጥ
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የጌታ ራት
    ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
  • ሕይወትህን የሚነካ በዓል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2004
  • የጌታ ራት
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ይሖዋንና ልጁን ማስታወስ
    ከታላቁ አስተማሪ ተማር
ለተጨማሪ መረጃ
የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
my ታሪክ 99

ምዕራፍ 99

ፎቅ ላይ በሚገኝ አንድ ክፍል ውስጥ

ሐሙስ ማታ ነው፤ ከሁለት ቀናት በኋላ መሆኑ ነው። ኢየሱስና 12 ሐዋርያቱ የማለፍን በዓል ለማክበር የተዘጋጀውን እራት ለመብላት ፎቅ ላይ ወደሚገኘው ወደዚህ ሰፊ ክፍል መጥተዋል። ወደ ውጪ እየወጣ ያለው ሰው አስቆሮቱ ይሁዳ ነው። ካህናቱ ኢየሱስን እንዴት ሊያገኙት እንደሚችሉ ሊነግራቸው እየሄደ ነው።

ይሁዳ ከአንድ ቀን በፊት ወደ ካህናቱ ሄዶ ‘ኢየሱስን ለመያዝ እንድትችሉ ብረዳችሁ ምን ትሰጡኛላችሁ?’ ብሎ ጠይቋቸው ነበር። ‘ሠላሳ የብር ሳንቲሞች እንሰጥሃለን’ አሉት። ስለዚህ ይሁዳ ሰዎቹን መርቶ ኢየሱስን ለማስያዝ እየሄደ ነው። አያሳዝንም?

የማለፍ በዓልን ለማክበር የተዘጋጀውን እራት ተመግበው ጨረሱ። ይሁን እንጂ ኢየሱስ ሌላ ልዩ እራት አዘጋጀ። ለሐዋርያቱ ዳቦ ሰጠና ‘ይህ ለእናንተ የሚሰጥ ሥጋዬ ነው፤ ብሉት’ አላቸው። ከዚያም ወይን ጠጅ ቀድቶ ሰጣቸውና ‘ይህ ለእናንተ የሚፈሰው ደሜ ነው፤ ጠጡት’ አላቸው። መጽሐፍ ቅዱስ ይህን ‘የጌታ እራት’ ብሎ ይጠራዋል።

እስራኤላውያን በግብፅ ሳሉ የአምላክ መልአክ የእነርሱን ቤቶች ‘አልፎ’ በግብፃውያን ቤቶች ውስጥ የሚገኙትን የበኩር ልጆች የገደለበትን ጊዜ ለማስታወስ የማለፍ በዓልን ያከብሩ ነበር። አሁን ግን ኢየሱስ ተከታዮቹ እሱንና ለእነርሱ ሕይወቱን አሳልፎ የሰጠበትን ሁኔታ እንዲያስታውሱ ለማድረግ ፈለገ። ይህን ልዩ በዓል በየዓመቱ እንዲያከብሩ ያዘዛቸውም በዚህ ምክንያት ነው።

የጌታን እራት ከበሉ በኋላ ኢየሱስ ተከታዮቹን ደፋር እንዲሆኑና ጠንካራ እምነት እንዲኖራቸው ነገራቸው። በመጨረሻም ለአምላክ ዘመሩና ወጡ። በዚህ ጊዜ በጣም መሽቶ ነበር፤ እኩለ ሌሊት ሳያልፍ አይቀርም። ወዴት እንደሚሄዱ እስቲ እንመልከት።

ማቴዎስ 26:​14-30፤ ሉቃስ 22:​1-39፤ ዮሐንስ ምዕራፍ 13 እስከ 17፤ 1 ቆሮንቶስ 11:​20

የአንቀጾቹ ጥያቄዎች

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ