የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • my ታሪክ 100
  • ኢየሱስ በአንድ የአትክልት ቦታ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ኢየሱስ በአንድ የአትክልት ቦታ
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ክርስቶስ አልፎ ተሰጠ እንዲሁም ተያዘ
    ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
  • በይሁዳ ጠቋሚነት መያዝ
    እስከ ዛሬ ከኖሩት ሁሉ የሚበልጠው ታላቅ ሰው
  • ኢየሱስ ታሰረ
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ያለብንን ፍርሃት ለማሸነፍ የሚያስችል እርዳታ
    ከታላቁ አስተማሪ ተማር
ለተጨማሪ መረጃ
የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
my ታሪክ 100

ምዕራፍ 100

ኢየሱስ በአንድ የአትክልት ቦታ

ኢየሱስና ሐዋርያቱ ፎቅ ላይ ከሚገኘው ክፍል ወጥተው ወደ ጌቴሴማኒ የአትክልት ቦታ ሄዱ። ከዚህ በፊት እዚህ ቦታ ብዙ ጊዜ መጥተዋል። ኢየሱስ ንቁ እንዲሆኑና እንዲጸልዩ ነገራቸው። ከዚያም ትንሽ ራቅ አለና መሬት ላይ ተደፍቶ ጸለየ።

በኋላ ኢየሱስ ሐዋርያቱ ወዳሉበት ቦታ ተመለሰ። ምን እያደረጉ የነበረ ይመስልሃል? ተኝተው ነበር! ኢየሱስ ነቅተው እንዲጠብቁ ሦስት ጊዜ የነገራቸው ቢሆንም ወደ እነርሱ በተመለሰ ቁጥር ተኝተው ያገኛቸው ነበር። ኢየሱስ መጨረሻ ወደ እነርሱ ተመልሶ ሲመጣ ‘በእንዲህ ያለ አስጨናቂ ጊዜ ላይ እንዴት ትተኛላችሁ? ለጠላቶቼ የምሰጥበት ሰዓት ደርሷል’ አላቸው።

ወዲያውኑ የብዙ ሰዎች ድምፅ ተሰማ። ተመልከት! ሰዎቹ ሰይፍና ዱላ ይዘው እየመጡ ነው! በደንብ እንዲታያቸውም ችቦ ይዘዋል። እየቀረቡ ሲመጡ ከመካከላቸው አንዱ ፈንጠር ብሎ ወጣና በቀጥታ ወደ ኢየሱስ መጣ። ሥዕሉ ላይ እንደምታየው ኢየሱስን ሳመው። ሰውየው አስቆሮቱ ይሁዳ ነው! ኢየሱስን የሳመው ለምንድን ነው?

ኢየሱስ ‘ይሁዳ ሆይ፣ በመሳም አሳልፈህ ትሰጠኛለህን?’ ሲል ጠየቀው። አዎ፣ ይሁዳ ኢየሱስን መሳሙ አንድ ምልክት ነበር። ከይሁዳ ጋር ያሉት ሰዎች የሚፈልጉት ሰው ማለትም ኢየሱስ የትኛው እንደሆነ መለየት ያስችላቸዋል። ስለዚህ የኢየሱስ ጠላቶች እርሱን ለመያዝ ተጠጉ። ይሁን እንጂ ጴጥሮስ ኢየሱስን ሲወስዱት ዝም ብሎ መመልከት አልፈለገም። ይዞት የመጣውን ሰይፍ መዘዘና አጠገቡ ያለውን ሰው መታው። ሰይፉ የሰውየውን ጭንቅላት ለትንሽ ስቶ የቀኝ ጆሮውን ቆረጠው። ሆኖም ኢየሱስ የሰውየውን ጆሮ ዳሰሰውና ፈወሰው።

ኢየሱስ ጴጥሮስን ‘ሰይፍህን ወደ ቦታው መልስ። አባቴ እኔን ለማዳን በሺህ የሚቆጠሩ መላእክትን እንዲልክልኝ ልጠይቀው እንደምችል አታውቅምን?’ አለው። አዎ፣ ኢየሱስ መጠየቅ ይችል ነበር! ሆኖም ኢየሱስ ጠላቶቹ እሱን የሚወስዱበት ጊዜ እንደደረሰ ያውቅ ስለነበረ አምላክን መላእክት እንዲልክለት አልጠየቀውም። ስለዚህ ይዘውት እንዲሄዱ ፈቀደላቸው። ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ምን እንደደረሰበት እስቲ እንመልከት።

ማቴዎስ 26:​36-56፤ ሉቃስ 22:​39-53፤ ዮሐንስ 18:​1-12

የአንቀጾቹ ጥያቄዎች

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ