የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • sp ገጽ 28-29
  • አስደናቂ የወደፊት ተስፋ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አስደናቂ የወደፊት ተስፋ
  • የሙታን መናፍስት—ሊረዱህ ወይም ሊጎዱህ ይችላሉን? ደግሞስ በእርግጥ አሉን?
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ሙታን እንደገና በሕይወት ይኖራሉ!
  • የአንባቢያን ጥያቄዎች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2004
  • የእባቡን ጭንቅላት መቀጥቀጥ
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
  • ኢየሱስ ከአጋንንት የበለጠ ኃይል አለው
    ከታላቁ አስተማሪ ተማር
  • መለኮታዊ ትምህርትና የአጋንንት ትምህርት የሚያደርጉት ውጊያ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1994
ለተጨማሪ መረጃ
የሙታን መናፍስት—ሊረዱህ ወይም ሊጎዱህ ይችላሉን? ደግሞስ በእርግጥ አሉን?
sp ገጽ 28-29

አስደናቂ የወደፊት ተስፋ

ኢየሱስ ሰይጣንን ወደ ጥልቁ ሲወረውረው

በቅርቡ ሰይጣንና አጋንንት ከሥራ ይታገዳሉ

ሰይጣንና አጋንንቱ ከአሁን ወዲያ ሰዎችን የሚያሳስቱበት ረጅም ጊዜ የላቸውም። ቀደም ብሎም ይሖዋ ከሰማይ አውጥቶ ጥሏቸዋል። (ራእይ 12:9) በቅርቡ ደግሞ አምላክ በሰይጣንና በአጋንንቱ ላይ እርምጃ ይወስዳል። ሐዋርያው ዮሐንስ ከአምላክ በተሰጠው ራእይ እንደሚከተለው ብሏል፦ “እኔም የጥልቁን ቁልፍና ታላቅ ሰንሰለት በእጁ የያዘ አንድ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ። እሱም ዘንዶውን ያዘውና ለ1,000 ዓመት አሰረው፤ ይህም ዘንዶ ዲያብሎስና ሰይጣን የሆነው የጥንቱ እባብ ነው። ደግሞም ይህ 1,000 ዓመት እስኪያበቃ ድረስ ከእንግዲህ ሕዝቦችን እንዳያሳስት ወደ ጥልቁ ወረወረውና ዘጋበት፤ በማኅተምም አሸገው።” (ራእይ 20:1-3) በኋላም ዲያብሎስና አጋንንቱ ለዘላለም ይጠፋሉ።—ራእይ 20:10

በምድር ላይ ያሉት መጥፎ ሰዎችም ይጠፋሉ።—መዝሙር 37:9, 10፤ ሉቃስ 13:5

ሙታን እንደገና በሕይወት ይኖራሉ!

ገነት በሆነችው ምድር ላይ ሰዎች ሙታንን በትንሣኤ ሲቀበሉ

ሙታን ወደ ሕይወት ተመልሰው በምድር ላይ ይኖራሉ

ሰይጣንና አጋንንቱ ከተወገዱ በኋላ ይሖዋ ለሰው ልጆች ብዙ በረከቶች ያመጣላቸዋል። ሙታን አሁን ሕይወት እንደሌላቸውና በሕይወት እንደማይኖሩ ከመጽሐፍ ቅዱስ የተማርከውን ታስታውሳለህ። ኢየሱስ ሞትን ከእንቅልፍ ማለትም ሕልም ከሌለበት ከከባድ እንቅልፍ ጋር አመሳስሏል። (ዮሐንስ 11:11-14) እንዲህ ያደረገው በሞት ያንቀላፉት ተቀስቅሰው ወደ ሕይወት እንደሚመለሱ ያውቅ ስለነበረ ነው። “በመታሰቢያ መቃብር ያሉ ሁሉ . . . ይወጣሉ” ብሏል።—ዮሐንስ 5:28, 29፤ ከሐዋርያት ሥራ 24:15 ጋር አወዳድር።

ሙታን ወደ ሕይወት ተመልሰው የሚኖሩት እዚችው ምድር ላይ ነው። የሞቱ ሰዎችን ስም ዝርዝር በሚገልጹ የመርዶ ማስታወቂያዎች ፈንታ ወደ ሕይወት ስለተመለሱት ሰዎች የሚናገሩ አስደሳች ሪፖርቶች ይሰማሉ! የሚወዱትን ሰው ከመቃብር ሲወጣ ተቀብሎ ማስተናገድ ምን ያህል ያስደስት ይሆን!

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ