የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • yp2 ገጽ 287
  • አርዓያ የሚሆኑ ሰዎች​—አሳፍ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አርዓያ የሚሆኑ ሰዎች​—አሳፍ
  • ወጣቶች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎችና ተግባራዊ መሆን የሚችሉ መልሶች፣ ጥራዝ 2
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ብልጽግና እምነትህን ሊፈትነው ይችላል
    መጠበቂያ ግንብ—1993
  • አሉታዊ ስሜቶችን መቋቋም የሚቻለው እንዴት ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2001
  • ድርሻዬ ይሖዋ ነው
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2011
  • ክርስቲያኖች—በማንነታችሁ ልትኮሩ ይገባል!
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2005
ለተጨማሪ መረጃ
ወጣቶች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎችና ተግባራዊ መሆን የሚችሉ መልሶች፣ ጥራዝ 2
yp2 ገጽ 287

አርዓያ የሚሆኑ ሰዎች​—አሳፍ

አሳፍ ግራ የሚያጋባ ሁኔታ አጋጥሞታል። በዙሪያው የሚያያቸው ሰዎች የአምላክን ሕግጋት ቢጥሱም መጥፎ ነገር የሚደርስባቸው አይመስልም! በዚህም የተነሳ አሳፍ፣ አምላክን ለማስደሰት መጣሩ ምንም ዋጋ እንደሌለው ይሰማው ጀመር። “ለካ ልቤን ንጹሕ ያደረግሁት በከንቱ ነው፤ እጄንም በየዋህነት የታጠብሁት በከንቱ ኖሮአል!” አለ። ይሁንና አሳፍ በጉዳዩ ላይ በደንብ ሲያስብበት አመለካከቱን አስተካከለ። ክፉዎች የሚያገኙት ማንኛውም ደስታ ጊዜያዊ እንደሆነ ተገነዘበ። ታዲያ ምን መደምደሚያ ላይ ደረሰ? “በምድርም ከአንተ ሌላ የምሻው [“ደስ የሚያሰኘኝ፣” NW] የለኝም” በማለት ለይሖዋ በመዝሙር ነግሮታል።—መዝሙር 73:3, 13, 16, 25, 27

አንተም የአምላክን መመሪያዎች መከተል ጠቃሚ መሆኑን የተጠራጠርክባቸው ጊዜያት ይኖሩ ይሆናል። ላይ ላዩን የምታየው ነገር አያታልህ፤ ከዚህ ይልቅ እንደ አሳፍ ነገሩን በጥልቅ አስብበት። የይሖዋን ሕግጋት ችላ ያሉ ሰዎች ሕይወታቸው ምን እንደሚመስል አስተውል። እውነት ሰላም አላቸው? እነዚህ ሰዎች፣ ታማኝ የአምላክ አገልጋዮች የማያውቁት ለደስታ ቁልፍ የሆነ ነገር አግኝተዋል? ነገሩን በጥሞና ካሰብክበት አንተም እንደ አሳፍ ‘ለእኔ ግን ወደ አምላክ መቅረብ ይሻለኛል’ እንደምትል ምንም ጥርጥር የለውም።—መዝሙር 73:28

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ