መዝሙር 135
እስከ መጨረሻው መጽናት
በወረቀት የሚታተመው
1. ለመጽናት ምክንያት ይሆናል፣
አምላክ የገባው ቃል።
አንተን የማረከህ እውነት
ነው እምነት ’ሚጣልበት።
ያምላክን ቀን እይ አቅርበህ፤
ጸንተህ ኑር በእምነትህ።
በታማኝነት ስትጸና
ያጠራሃል ፈተና።
2. የቀድሞ ፍቅርህን ጠብቅ፤
ስለሚችል ላይዘልቅ።
ፈተናው ከባድ ቢሆንም
ተወጣው እንደምንም።
ምንም ችግር ቢያጋጥምህ
ጥርጣሬ አይግባህ።
አምላክ መውጫ ያዘጋጃል፤
ያኔ አለሁ ይልሃል።
3. እስከ ፍጻሜው ’ሚጸኑ
ሁሉ ይድናሉ።
ባምላክ የሕይወት መጻፍ ላይ
በደማቅ ይጻፋሉ።
ጸንቶ መቆም ግብህ ይሁን፤
ጽናት ይሥራ ሥራውን።
አምላክ ሞገስ ይሰጥሃል፤
ደስተኛ ያደርግሃል።
(በተጨማሪም ዕብ. 6:19ን፣ ያዕ. 1:4ን፣ 2 ጴጥ. 3:12ን እና ራእይ 2:4ን አንብብ።)