የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • hf ክፍል 4 ገጽ 12-14
  • የገንዘብ አያያዝ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የገንዘብ አያያዝ
  • ደስተኛ ቤተሰብ ሊኖርህ ይችላል
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • 1 በጥንቃቄ ዕቅድ አውጡ
  • 2 ግልጽና ምክንያታዊ ሁኑ
  • የገንዘብ አያያዝ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2009
  • ለገንዘብ ሚዛናዊ አመለካከት ይኑርህ
    ንቁ!—2015
  • ገንዘብ
    ንቁ!—2014
  • ገንዘብ የክፋት ሁሉ ሥር ነው?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
ለተጨማሪ መረጃ
ደስተኛ ቤተሰብ ሊኖርህ ይችላል
hf ክፍል 4 ገጽ 12-14
አንድ ባልና ሚስት ገንዘባቸውን እንዴት እንደሚጠቀሙበት በጥንቃቄ ዕቅድ ሲያወጡ

ክፍል 4

የገንዘብ አያያዝ

“መመካከር ሲኖር የታቀደው ነገር ይሳካል።”—ምሳሌ 20:18

ሁላችንም ብንሆን ለቤተሰባችን የሚያስፈልጉ ነገሮችን ለማሟላት ገንዘብ ያስፈልገናል። (ምሳሌ 30:8) ደግሞም “ገንዘብ ጥበቃ” ያስገኛል። (መክብብ 7:12) ከትዳር ጓደኛችሁ ጋር ስለ ገንዘብ መነጋገር አስቸጋሪ ሊሆን ቢችልም ገንዘብ በትዳራችሁ ውስጥ ችግር እንዲፈጥር አትፍቀዱ። (ኤፌሶን 4:32) ባልና ሚስት ገንዘባቸውን እንዴት ማውጣት እንዳለባቸው በሚወስኑበት ጊዜ እርስ በርስ መተማመንና መተባበር ይኖርባቸዋል።

1 በጥንቃቄ ዕቅድ አውጡ

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? “ከእናንተ መካከል፣ ግንብ ለመገንባት ፈልጎ ለመጨረስ የሚያስችል በቂ ገንዘብ እንዳለው ለማወቅ በመጀመሪያ ተቀምጦ ወጪውን የማያሰላ ማን ነው?” (ሉቃስ 14:28) ገንዘባችሁን እንዴት እንደምትጠቀሙበት አንድ ላይ ሆናችሁ ዕቅድ ማውጣታችሁ አስፈላጊ ነው። (አሞጽ 3:3) ምን መግዛት እንደሚያስፈልጋችሁና ማውጣት የምትችሉት ምን ያህል እንደሆነ ወስኑ። (ምሳሌ 31:16) አንድን ነገር ለመግዛት የሚያስችል ገንዘብ ስላላችሁ ብቻ የግድ መግዛት ይኖርባችኋል ማለት አይደለም። ዕዳ ውስጥ ላለመግባት ተጠንቀቁ። በእጃችሁ ካለው ገንዘብ በላይ አታውጡ።—ምሳሌ 21:5፤ 22:7

ምን ማድረግ ትችላላችሁ?

  • አስፈላጊ የሆኑ ወጪዎችን ሁሉ ከሸፈናችሁ በኋላ በተረፈው ገንዘብ ምን እንደምታደርጉበት አንድ ላይ ሆናችሁ ወስኑ

  • ወጪያችሁ ከገቢያችሁ ከበለጠ ወጪያችሁን ለመቀነስ ምን እንደምታደርጉ ግልጽ የሆነ ዕቅድ አውጡ። ለምሳሌ ያህል፣ ምግብ ቤት በመብላት ፋንታ ቤት ውስጥ ምግብ ማዘጋጀት ትችላላችሁ

አንድ ባልና ሚስት ከበድ ስላሉ ወጪዎቻቸው ሲያስቡ

2 ግልጽና ምክንያታዊ ሁኑ

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? “በይሖዋ ፊት ብቻ ሳይሆን በሰዎችም ፊት ሁሉንም ነገር በሐቀኝነት [አከናውኑ]።” (2 ቆሮንቶስ 8:21) ገቢና ወጪህን በተመለከተ ለትዳር ጓደኛህ ሐቀኛ ሁን።

ከገንዘብ ጋር የተያያዘ ከበድ ያለ ውሳኔ ስታደርግ ምንጊዜም ከትዳር ጓደኛህ ጋር ተመካከር። (ምሳሌ 13:10) ስለ ገንዘብ መነጋገራችሁ በትዳራችሁ ውስጥ ሰላም እንዲኖር ይረዳል። ገቢህን እንደ ግል ገንዘብህ ሳይሆን እንደ ቤተሰቡ ገንዘብ አድርገህ ተመልከተው።—1 ጢሞቴዎስ 5:8

አንድ ባልና ሚስት ገበያ ወጥተው እያለ፣ የጻፉትን ዝርዝር ሲመለከቱ

ምን ማድረግ ትችላላችሁ?

  • አንዳችሁ ሌላውን ሳታማክሩ ምን ያህል ገንዘብ ማውጣት እንደምትችሉ ተነጋግራችሁ ወስኑ

  • ስለ ገንዘብ ለመነጋገር ችግር እስኪፈጠር አትጠብቁ

ለገንዘብ ያላችሁ አመለካከት

ገንዘብ ጠቃሚ ቢሆንም ትዳራችሁን እንዲበጠብጥ ወይም አላስፈላጊ ጭንቀት እንዲፈጥርባችሁ አትፍቀዱለት። (ማቴዎስ 6:25-34) በሕይወት ለመደሰት ብዙ ገንዘብ አያስፈልጋችሁም። መጽሐፍ ቅዱስ “ከስግብግብነትም ሁሉ ተጠበቁ” ይላል። (ሉቃስ 12:15) ገንዘብ ሊገዛው የሚችል ማንኛውም ውድ ነገር ከትዳራችሁ ሊበልጥ አይችልም። በመሆኑም ባላችሁ ነገር ረክታችሁ ኑሩ፤ እንዲሁም ከአምላክ ጋር ያላችሁን ዝምድና ፈጽሞ ችላ አትበሉ። ይህን ካደረጋችሁ ቤተሰባችሁ ደስተኛ ይሆናል፤ ብሎም የይሖዋን ሞገስ ታገኛላችሁ።—ዕብራውያን 13:5

ራስህን እንዲህ እያልክ ጠይቅ፦

  • ዕዳ ውስጥ ላለመግባት በቤተሰብ ደረጃ ምን ማድረግ እንችላለን?

  • እኔና ባለቤቴ ስለ ገንዘብ በግልጽ ከተወያየን ምን ያህል ጊዜ ሆኖናል?

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ