የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • jy ምዕ. 47 ገጽ 118-ገጽ 119 አን. 6
  • አንዲት ልጅ ከሞት ተነሳች!

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አንዲት ልጅ ከሞት ተነሳች!
  • ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ለቅሶ ወደ ታላቅ ደስታ ተለወጠ
    እስከ ዛሬ ከኖሩት ሁሉ የሚበልጠው ታላቅ ሰው
  • ኢየሱስ የሞቱ ሰዎችን አስነሳ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ከሞት ልንነሳ እንችላለን!
    ከታላቁ አስተማሪ ተማር
  • ኢየሱስ ብዙ ተአምራት ፈጽሟል
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
ለተጨማሪ መረጃ
ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
jy ምዕ. 47 ገጽ 118-ገጽ 119 አን. 6
ኢየሱስ የኢያኢሮስን ልጅ ከሞት አስነሳት

ምዕራፍ 47

አንዲት ልጅ ከሞት ተነሳች!

ማቴዎስ 9:18, 23-26 ማርቆስ 5:22-24, 35-43 ሉቃስ 8:40-42, 49-56

  • ኢየሱስ የኢያኢሮስን ልጅ አስነሳት

ኢያኢሮስ፣ ደም ይፈስሳት የነበረችውን ሴት ኢየሱስ እንደፈወሳት ሲመለከት የእሱንም ልጅ ሊያድናት እንደሚችል ተሰምቶት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። ይሁንና “እስካሁን ልጄ ሳትሞት አትቀርም” ብሎ አስቧል። (ማቴዎስ 9:18) ታዲያ ኢየሱስ ከዚህ በኋላ ሊረዳት ይችል ይሆን?

ኢየሱስ ከፈወሳት ሴት ጋር እየተነጋገረ ሳለ ከኢያኢሮስ ቤት የመጡ ሰዎች ኢያኢሮስን “ልጅህ ሞታለች! ከዚህ በኋላ መምህሩን ለምን ታስቸግረዋለህ?” አሉት።—ማርቆስ 5:35

ይህ እንዴት ያለ ከባድ መርዶ ነው! ኢያኢሮስ በማኅበረሰቡ ዘንድ በጣም የተከበረ ሰው ቢሆንም አሁን ግን ምንም ማድረግ አይችልም። አንዲት ልጁን በሞት አጥቷል። ይሁን እንጂ ኢየሱስ ሲነጋገሩ ስለሰማቸው ወደ ኢያኢሮስ ዞረና “አትፍራ፤ ብቻ እመን” በማለት አበረታታው።—ማርቆስ 5:36

በኢያኢሮስ ልጅ አስከሬን አቅራቢያ ሆነው የሚያለቅሱ ሐዘንተኞች

ከዚያም ኢየሱስ ከኢያኢሮስ ጋር በመሆን ወደ ቤቱ አመራ። በቦታው ሲደርሱ ከፍተኛ ትርምስ ተመለከቱ። በዚያ የተሰበሰቡት ሰዎች እያለቀሱ፣ ዋይ ዋይ እያሉና በሐዘን ደረታቸውን እየደቁ ነው። ኢየሱስ ወደ ውስጥ ሲገባ “ልጅቷ ተኝታለች እንጂ አልሞተችም” በማለት አስገራሚ ነገር ተናገረ። (ማርቆስ 5:39) ሰዎቹ ይህን ሲሰሙ ሳቁበት። ልጅቷ እንደሞተች ያውቃሉ። ይሁንና ሰዎችን ከከባድ እንቅልፍ የመቀስቀስ ያህል ኢየሱስ፣ አምላክ የሰጠውን ኃይል በመጠቀም የሞቱትን በቀላሉ ሊያስነሳ እንደሚችል ሊያሳያቸው ነው።

ኢየሱስ ከጴጥሮስ፣ ከያዕቆብ፣ ከዮሐንስና ከሞተችው ልጅ ወላጆች በስተቀር ሁሉንም ወደ ውጭ አስወጣ። ከአምስቱ ሰዎች ጋር ሆኖ ልጅቷ ወዳለችበት ገባ። ከዚያም “የልጅቷን እጅ ይዞ ‘ጣሊታ ቁሚ’ አላት፤ ትርጉሙም ‘አንቺ ልጅ፣ ተነሽ!’ ማለት ነው።” (ማርቆስ 5:41) ልጅቷም ወዲያው ተነስታ መራመድ ጀመረች። ኢያኢሮስና ባለቤቱ ይህን ሲያዩ ምን ያህል በደስታ እንደተዋጡ እስቲ አስበው! ኢየሱስ ለልጅቷ የምትበላው ነገር እንዲሰጧት መናገሩ ልጅቷ በእርግጥ ሕያው መሆኗን የሚያሳይ ተጨማሪ ማስረጃ ነው።

ከዚህ ቀደም ኢየሱስ የፈወሳቸውን ሰዎች ስለ ጉዳዩ ለሌሎች እንዳያወሩ ያዝዛቸው ነበር፤ ለኢያኢሮስና ለባለቤቱም ተመሳሳይ መመሪያ ሰጣቸው። ያም ቢሆን እጅግ የተደሰቱት የልጅቷ ወላጆችና ሌሎች ሰዎች ወሬውን “በዚያ አገር ሁሉ በሰፊው” አዳረሱት። (ማቴዎስ 9:26) አንተስ የምትወደው ሰው ከሞት ሲነሳ ብትመለከት ይህን ለማውራት አትጓጓም? ይህ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተመዝግቦ የምናገኘው ኢየሱስ የፈጸመው ሁለተኛው ትንሣኤ ነው።

  • ኢያኢሮስ ምን ወሬ ደረሰው? ኢየሱስ ያጽናናውስ እንዴት ነው?

  • ኢያኢሮስ ከኢየሱስ ጋር ሆኖ ቤቱ ሲደርስ ምን ሁኔታ አጋጠማቸው?

  • ኢየሱስ የሞተችው ልጅ እንደተኛች የተናገረው ለምንድን ነው?

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ