የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 4 ገጽ 16-ገጽ 17 አን. 2
  • ቃየን ተናዶ ወንድሙን ገደለው

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ቃየን ተናዶ ወንድሙን ገደለው
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የተለያየ አመለካከት ያዳበሩ ወንድማማቾች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
  • አንድ ጥሩ ልጅና አንድ መጥፎ ልጅ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • በይሖዋ ዘንድ ተቀባይነት ያለው መሥዋዕት ማቅረብ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1999
  • የአንባብያን ጥያቄዎች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 4 ገጽ 16-ገጽ 17 አን. 2
አቤል ለይሖዋ መባውን ሲያቀርብ ቃየን ተናደደ

ትምህርት 4

ቃየን ተናዶ ወንድሙን ገደለው

አዳምና ሔዋን ከኤደን የአትክልት ስፍራ ከወጡ በኋላ ብዙ ልጆችን ወለዱ። የመጀመሪያ ልጃቸው ቃየን ገበሬ ሆነ፤ ሁለተኛ ልጃቸው አቤል ደግሞ እረኛ ሆነ።

አንድ ቀን፣ ቃየንና አቤል ለይሖዋ መባ አቀረቡ። መባ ምን እንደሆነ ታውቃለህ? መባ ለአምላክ የሚሰጥ ስጦታ ነው። ይሖዋ አቤል ባቀረበው መባ የተደሰተ ቢሆንም ቃየን ባቀረበው መባ ግን አልተደሰተም። ይህም ቃየንን በጣም አናደደው። ይሖዋ ቃየንን ንዴቱ መጥፎ ነገር እንዲፈጽም ሊያደርገው እንደሚችል አስጠነቀቀው። ቃየን ግን ይሖዋ ያለውን አልሰማም።

ቃየን አቤልን “ና ወደ ሜዳ እንሂድ” አለው። ሜዳ ላይ ብቻቸውን ሳሉ ቃየን ወንድሙን መታውና ገደለው። በዚህ ጊዜ ይሖዋ ምን አደረገ? ይሖዋ ቃየንን ከቤተሰቡ ተለይቶ ወደ ሩቅ ቦታ እንዲሄድ በማድረግ ቀጣው። ቃየን ተመልሶ እንዳይመጣ ተከልክሎ ነበር።

ቃየንና አቤል ሜዳው ላይ ሲገናኙ

ከዚህ ታሪክ ምን ትምህርት እናገኛለን? አንዳንድ ነገሮች እኛ እንደፈለግነው ሳይሆኑ ሲቀሩ ልንናደድ እንችላለን። ሰዎች መናደዳችንን ተመልክተው ምክር ሊሰጡን ይችላሉ፤ ወይም ደግሞ እንደተናደድን እኛ ራሳችን ሊታወቀን ይችላል። በዚህ ጊዜ መጥፎ ነገር ከማድረጋችን በፊት ቶሎ ንዴታችንን ለማብረድ ጥረት ማድረግ አለብን።

አቤል ይሖዋን ይወድና ትክክል የሆነውን ነገር ያደርግ ስለነበር ይሖዋ ሁልጊዜም ያስታውሰዋል። አምላክ ምድርን ገነት ሲያደርግ አቤልን ከሞት ያስነሳዋል።

“በመጀመሪያ ከወንድምህ ጋር ታረቅ፤ ከዚያም ተመልሰህ መባህን አቅርብ።”—ማቴዎስ 5:24

ጥያቄ፦ አዳምና ሔዋን መጀመሪያ ላይ የወለዷቸው ሁለት ልጆች እነማን ነበሩ? ቃየን ወንድሙን የገደለው ለምንድን ነው?

ዘፍጥረት 4:1-12፤ ዕብራውያን 11:4፤ 1 ዮሐንስ 3:11, 12

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ