መዝሙር 131
“አምላክ ያጣመረውን”
በወረቀት የሚታተመው
1. በደስታ፣ በክብር
ተገመደ በሦስት።
ባምላክና በሰው ፊት፣
ቃል ኪዳን ገባላት።
(አዝማች 1)
በአምላክ ፊት ማለላት፤
ከልቡ ሊወዳት።
‘አምላክ ያጣመረውን፣
ማንም አይለያየው።’
2. መርምረዋል ቃሉን፤
ለማድረግ ፈቃዱን።
እርዳታውን ይሻሉ፤
ታማኞች ለመሆን።
(አዝማች 2)
በአምላክ ፊት ቃል ገባች፤
ከልቧ ልትወደው።
‘አምላክ ያጣመረውን፣
ማንም አይለያየው።’
(በተጨማሪም ዘፍ. 2:24ን፣ መክ. 4:12ን እና ኤፌ. 5:22-33ን ተመልከት።)