የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lvs ገጽ 3
  • የበላይ አካሉ መልእክት

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የበላይ አካሉ መልእክት
  • ከአምላክ ፍቅር ሳትወጡ ኑሩ
  • በከአምላክ ፍቅር አንብብ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የአምላክ ፍቅር ለዘላለም ይኖራል
    ከአምላክ ፍቅር ሳትወጡ ኑሩ
  • ከአምላክ ፍቅር አትውጣ
    ትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው?
  • ፍቅራችሁ እንዳይቀዘቅዝ ተጠንቀቁ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2017
  • “አምላክን መውደድ” ሲባል ምን ማለት ነው?
    ‘ከአምላክ ፍቅር አትውጡ’
ለተጨማሪ መረጃ
ከአምላክ ፍቅር ሳትወጡ ኑሩ
lvs ገጽ 3

የበላይ አካሉ መልእክት

ይሖዋ አምላክንና ቃሉን መጽሐፍ ቅዱስን ለምትወዱ ሁሉ፦

ኢየሱስ “እውነትንም ታውቃላችሁ፤ እውነትም ነፃ ያወጣችኋል” በማለት ተናግሯል። (ዮሐንስ 8:32) በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኘውን እውነት ለመጀመሪያ ጊዜ ስትማር ምን እንደተሰማህ እስቲ ለማስታወስ ሞክር። በሐሰት በተሞላ ዓለም ውስጥ እውነትን ማወቅ መቻል በጣም አስደሳች ነገር ነው!—2 ጢሞቴዎስ 3:1

ይሖዋ አምላክ እውነትን እንድናውቅ ይፈልጋል። እኛም ለሰዎች ፍቅር ስላለን ስለ እውነት ልንነግራቸው እንፈልጋለን። አምላክን ማገልገል ግን ከዚህ ያለፈ ነገር ማድረግን ይጨምራል። ለይሖዋ መሠረታዊ ሥርዓቶች ጥልቅ አክብሮት ስላለን ለክርስቲያኖች በሚገባ መንገድ ለመኖር የምንችለውን ያህል መጣር ይኖርብናል። አምላክን እንደምንወደው ማሳየት የምንችልበትን አንዱን መንገድ ኢየሱስ ገልጿል። እንዲህ ብሏል፦ “እኔ የአብን ትእዛዛት ጠብቄ በፍቅሩ እንደምኖር እናንተም ትእዛዛቴን ብትጠብቁ በፍቅሬ ትኖራላችሁ።”—ዮሐንስ 15:10

ኢየሱስ አባቱን በጣም ይወደዋል፤ አባቱ የሚያዘውን ነገር ሁሉ ያደርጋል። እኛም በአኗኗራችን የኢየሱስን ምሳሌ የምንከተል ከሆነ ይሖዋ ይወደናል፤ እውነተኛ ደስታም እናገኛለን። ኢየሱስ “እነዚህን ነገሮች ስለምታውቁ ብትፈጽሟቸው ደስተኞች ናችሁ” በማለት ተናግሯል።—ዮሐንስ 13:17

ይህ መጽሐፍ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በሚገኘው እውነት መሠረት ሕይወትህን ለመምራትና የአምላክ ወዳጅ ለመሆን እንዲረዳህ እንመኛለን። ለአምላክ ያለህ ፍቅር እያደገ እንዲሄድ እንዲሁም ‘የዘላለም ሕይወት የሚያስገኝልህን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት እየተጠባበቅክ ከአምላክ ፍቅር ሳትወጣ እንድትኖር’ ጸሎታችን ነው።—ይሁዳ 21

የይሖዋ ምሥክሮች የበላይ አካል

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ