መጽሔቶችን ለማበርከት ምን ማለት ይቻላል?
ንቁ!መስከ.2001
“እንደሚያውቁት ብዙዎቹ ወጣቶቻችን የወደፊት ሕይወታቸው ያሳስባቸዋል። አንዳንዶች በጣም ይጨነቃሉ። እርዳታ ማግኘት የሚችሉ ይመስልዎታል? [መልስ እንዲሰጥ ፍቀድለት።] ይህ መጽሔት ወጣቶችን ምን እንደሚያስጨንቃቸውና እንዴት መርዳት እንደሚቻል ይናገራል።”
መጠበቂያ ግንብ መስከ. 15
“በሁሉም ሃይማኖቶች ውስጥ ለማለት ይቻላል እውነትን የሚያፈቅሩ ሰዎች አሉ። ሆኖም በጥቅሉ ሃይማኖት ሰዎችን የመከፋፈል አዝማሚያ ይታይበታል። ቅን ልብ ያላቸውን ሰዎች አንድ ለማድረግ ምን መደረግ ይኖርበታል? [መልስ ከሰጠ በኋላ ሶፎንያስ 3:9ን አንብብ።] ይህ መጽሔት ከእውነተኛው አምላክ የሚገኘው እውቀት በየትኛውም ሥፍራ የሚኖሩ ሰዎችን እንዴት አንድ እያደረገ እንዳለ ይገልጻል።”
ንቁ!ጥቅ. 2001
“ብዙዎቻችን የሚበላ ነገር እንደልብ የመገኘቱን ጉዳይ እምብዛም ትኩረት ሰጥተን አስበንበት አናውቅም። ሆኖም አሁን አሁን ሳይንስ በምግብ አቅርቦት ላይ አደጋ እየፈጠረ ይሆን የሚል ስጋት አለ። ይህ መጽሔት አሳሳቢ ሆነው የተገኙት አንዳንድ ችግሮች ምን እንደሆኑና ለችግሩ እንዴት እውነተኛ መፍትሔ እንደሚገኝ መጽሐፍ ቅዱስ የሚሰጠውን ተስፋ ይገልጻል።”
መጠበቂያ ግንብ ጥቅ. 1
“አሁን አሁን ብዙ ሰዎች በአምላክ ስለማመን መወያየት አይፈልጉም ቢባል ሳይስማሙ አይቀሩም። ሆኖም ይህ የሆነው ለምንድን ነው? [መልሱን ከሰማህ በኋላ ዕብራውያን 11:1ን አንብብ።] ይህ መጽሔት እውነተኛ እምነት ምን እንደሆነና እምነት ያለን መሆን አለመሆኑ ምን ለውጥ እንደሚያመጣ ይገልጻል።”