የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 7/02 ገጽ 3
  • ‘ሁልጊዜ መልካም ለማድረግ ትጉ’

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ‘ሁልጊዜ መልካም ለማድረግ ትጉ’
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2002
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • መልካም በማድረግ ምሳሌ ሁኑ
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2003
  • የ2008 የይሖዋ ምሥክሮች የአውራጃ ስብሰባ
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2008
  • የቤተሰብ ደስታ—ከተባለው መጽሐፍ በጉባኤ ለሚደረገው የመጽሐፍ ጥናት የወጣ ፕሮግራም
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2001
  • “በአሕዛብ መካከል መልካም ምግባር ይዛችሁ ኑሩ”
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2014
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2002
km 7/02 ገጽ 3

‘ሁልጊዜ መልካም ለማድረግ ትጉ’

1 ክርስቲያናዊ ሕይወት ለሰው ‘ሁሉ መልካም ለማድረግ መትጋትን’ የሚጠይቅ ነው። (1 ተ⁠ሰ. 5:15) በአውራጃ ስብሰባዎች ላይ ስንገኝ ለሌሎች መልካም ማድረግ የምንችልባቸው በርካታ አጋጣሚዎች እናገኛለን። እንዲህ ባሉት ጊዜያት ሰዎች ስለ እኛ ብዙ ነገሮችን ማስተዋል እንዲሁም እነርሱን ከምንይዝበት መንገድ በመነሳት ስለ እኛ አንድ ዓይነት ድምዳሜ ላይ ሊደርሱ ይችላሉ። የይሖዋ ምሥክር እንደመሆናችን መጠን መልካም ስማችንን ጠብቀን ለመኖር ‘ሁሉን ሰው እንደምናከብር’ በድርጊታችን ማሳየት ያስፈልገናል። (1 ጴ⁠ጥ. 2:17) ይህም ‘ለራሳችን የሚጠቅመንን ሳይሆን የሌሎችን ጥቅም መመልከትን’ ይጨምራል። (ፊልጵ. 2:4) ይህ የልጆቻችንን ጠባይ በተመለከተ እንዴት እንደሚሠራ እንመልከት።

2 ልጆቻችን መልካም እንዲያደርጉ ማስተማር፦ ወላጆቻቸው በቅርብ የማይከታተሏቸው አንዳንድ ልጆች ችግሮች ሲፈጥሩ ይታያሉ። (ምሳሌ 29:15) አንዳንድ ጊዜ ይህ የሚሆነው ወላጆች በሌሎች ጉዳዮች ተጠምደው ልጆቻቸውን ሳይቆጣጠሩ ስለሚቀሩ ነው። በዚህ ምክንያት አንዳንድ ልጆች በጣም የሚረብሹ ከመሆናቸው የተነሳ ምሥክሮችንም ሆነ ምሥክር ያልሆኑ ሌሎች ሰዎችን ያስቸግራሉ።

3 ወላጆች፣ ልጆቻችሁ በማንኛውም ጊዜና ቦታ ምን ዓይነት ክርስቲያናዊ ባሕርይ ሊያሳዩ እንደሚገባ ከአውራጃ ስብሰባው በፊት ጊዜ ወስዳችሁ ብታነጋግሯቸው ጥሩ ይሆናል። (ኤፌ. 6:4) ለምሳሌ ያህል፣ እውነተኛ የሆነ ክርስቲያናዊ ፍቅር ‘የማይገባውን እንደማያደርግ፣ የራሱን ጥቅም እንደማይፈልግ፣ እንደማይበሳጭ’ አሳዩአቸው። (1 ቆ⁠ሮ. 13:5) አዋቂዎች ለሁሉም መል​ካም አርዓያ በመሆን ለእነዚህ ቃላት አጽንዖት ሊሰጡ ይችላሉ። ልጆች፣ ወላጆቻችሁን በመታዘዝ፣ የሌሎችን ንብረት ላለማበላሸት ጥንቃቄ በማድረግና አብረዋችሁ ላሉት አሳቢነት በማሳየት መልካም ማድረግ ትችላላችሁ። (ቆላ. 3:20) በአንድነት ለሰዎች ሁሉ መልካም ለማድረግ ስንጥር ‘ስለ አዳኛችን ስለ እግዚአብሔር የሚሆነውን ትምህርት በሁሉ ነገር እናስመሰግናለን።’​—⁠ቲቶ 2:9-10

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ