የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w21 ታኅሣሥ ገጽ 14
  • የአንባቢያን ጥያቄዎች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአንባቢያን ጥያቄዎች
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2021
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የዘሌዋውያን መጽሐፍ ሌሎችን ስለምንይዝበት መንገድ ምን ያስተምረናል?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2021
  • ለዲያብሎስ ስፍራ አትስጡት
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2006
  • “ቅዱሳን ሁኑ”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2021
  • “ስምህ ይቀደስ”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2021
w21 ታኅሣሥ ገጽ 14
አንዲት እህት በጉባኤው ውስጥ ያለችን እህት በተመለከተ ለሌላ እህት መጥፎ ነገር ስትናገር።

የአንባቢያን ጥያቄዎች

በዘሌዋውያን 19:16 ላይ የሚገኘው “በባልንጀራህ ሕይወት ላይ አትነሳ” የሚለው ትእዛዝ ምን ትርጉም አለው? እኛስ ከዚህ ጥቅስ ምን ትምህርት እናገኛለን?

ይሖዋ እስራኤላውያንን ቅዱስ ሕዝብ እንዲሆኑ አሳስቧቸው ነበር። ይህን ማድረግ እንዲችሉም የሚከተለውን መመሪያ ሰጥቷቸዋል፦ “በሕዝብህ መካከል እየዞርክ ስም አታጥፋ። በባልንጀራህ ሕይወት ላይ አትነሳ። እኔ ይሖዋ ነኝ።”—ዘሌ. 19:2, 16

“አትነሳ” የሚለው ቃል እዚህ ቦታ ላይ የሚገኘውን የዕብራይስጥ ፈሊጣዊ አነጋገር ጥሩ አድርጎ ይገልጸዋል። ይሁንና ይህ አገላለጽ ምን ትርጉም አለው? የዘሌዋውያን መጽሐፍን የሚያብራራ አንድ የአይሁዳውያን የማመሣከሪያ ጽሑፍ እንዲህ ይላል፦ “ይህን የጥቅሱን ክፍል ማብራራት ያስቸግራል፤ ምክንያቱም የዕብራይስጡ ፈሊጣዊ አነጋገር ያለውን ትክክለኛ ትርጉም ማወቅ አስቸጋሪ ነው፤ ይህ አገላለጽ ቃል በቃል ቢፈታ ‘[በባልንጀራህ ሕይወት] ላይ፣ አጠገብ፣ አቅራቢያ አትቁም’ ማለት ነው።”

አንዳንድ ምሁራን ይህ ሐሳብ ከቁጥር 15 ጋር ተዛማጅነት እንዳለው ያስባሉ፤ ጥቅሱ “ፍርድ አታዛቡ። ለድሃው አታዳላ ወይም ባለጸጋውን ከሌሎች አስበልጠህ አትመልከት። ለባልንጀራህ ፍትሐዊ ፍርድ ፍረድ” ይላል። (ዘሌ. 19:15) እነዚህ ምሁራን እንደሚሉት ከሆነ፣ በቁጥር 16 ላይ የሚገኘው ‘በባልንጀራህ ላይ አትነሳ’ የሚለው ሐሳብ የአምላክ ሕዝቦች ከፍርድ ጉዳዮች፣ ከንግድ እንቅስቃሴዎች ወይም ከቤተሰባቸው ጋር በተያያዘ ፍትሕን ማጓደል እንደሌለባቸው የሚገልጽ ነው ማለት ነው፤ በተጨማሪም አንድ እስራኤላዊ ጥቅም ለማግኘት ሲል ሐቀኝነት የጎደለው ነገር ከማድረግ መቆጠብ እንዳለበት የሚጠቁም ነው። እነዚህን ነገሮች ማድረግ እንደሌለብን ጥያቄ የለውም። ይሁንና በቁጥር 16 ላይ የሚገኘው ሐሳብ ይበልጥ አሳማኝ የሆነ ሌላ ማብራሪያ ሊኖረው ይችላል።

በቁጥር 16 መጀመሪያ ላይ የሚገኘውን ሐሳብ እስቲ እንመልከት። አምላክ፣ እየዞሩ ስም እንዳያጠፉ ሕዝቡን አዟቸው ነበር። ስም ማጥፋት ከሐሜት የከፋ እንደሆነ እናስታውስ፤ እርግጥ ነው፣ ሐሜትም ቢሆን ጉዳት አለው። (ምሳሌ 10:19፤ መክ. 10:12-14፤ 1 ጢሞ. 5:11-15፤ ያዕ. 3:6) ስም አጥፊ የሚባለው ግን የሌላውን ሰው መልካም ስም ለማበላሸት ሲል ሆን ብሎ ውሸት የሚናገር ሰው ነው። ስም አጥፊ የሆነ ሰው የሌላን ሰው ሕይወት አደጋ ላይ ሊጥል እንደሚችል እያወቀም እንኳ የሐሰት ምሥክርነት ይሰጥ ይሆናል። ስም አጥፊ የሆኑ ሰዎች በናቡቴ ላይ በሐሰት እንደመሠከሩበት እናስታውሳለን፤ በዚህም የተነሳ ናቡቴ ያለጥፋቱ በድንጋይ ተወግሮ ተገድሏል። (1 ነገ. 21:8-13) በእርግጥም በዘሌዋውያን 19:16 ላይ እንደተገለጸው፣ ስም አጥፊ የሆነ ሰው በባልንጀራው ሕይወት ላይ ተነስቷል ሊባል ይችላል።

ከዚህም ሌላ አንድ ሰው የሌላውን ሰው ስም ማጥፋቱ ግለሰቡን እንደሚጠላው የሚጠቁም ሊሆን ይችላል። አንደኛ ዮሐንስ 3:15 እንዲህ ይላል፦ “ወንድሙን የሚጠላ ሁሉ ነፍሰ ገዳይ ነው፤ ነፍሰ ገዳይ የሆነ ሁሉ ደግሞ የዘላለም ሕይወት እንደሌለው ታውቃላችሁ።” አምላክ በቁጥር 16 ላይ የሚገኘውን መመሪያ ከሰጠ በኋላ በቀጣዩ ቁጥር ላይ “ወንድምህን በልብህ አትጥላው” በማለት መናገሩ ትኩረት የሚስብ ነው።—ዘሌ. 19:17

ከዚህ አንጻር፣ በዘሌዋውያን 19:16 ላይ የሚገኘው ሐሳብ ለክርስቲያኖች ጠንከር ያለ ምክር የያዘ ነው። ስለ ሌላ ሰው መጥፎ ነገር ከማሰብ ወይም ስሙን ከማጥፋት መቆጠብ አለብን። አንድ ሰው ደስ ስለማይለን ወይም በምቀኝነት ተነሳስተን ስሙን በማጥፋት በእሱ ላይ ‘ከተነሳን’ ይህ ግለሰቡን እንደምንጠላው የሚያሳይ ሊሆን ይችላል። ክርስቲያኖች ማንንም ላለመጥላት በጣም መጠንቀቅ ይኖርባቸዋል።—ማቴ. 12:36, 37

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ