የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • wp25 ቁጥር 1 ገጽ 4-5
  • ጦርነት እና ግጭት ሁላችንንም የሚነካን እንዴት ነው?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ጦርነት እና ግጭት ሁላችንንም የሚነካን እንዴት ነው?
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2025
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ውጊያው የሚያበቃው መቼ ነው?—መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
    ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
  • ጦርነት የሚያስከትለው ኪሳራ የገንዘብ ብቻ ነው?
    ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
  • ጦርነት እና ግጭት የሚቀረው እንዴት ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2025
  • ጦርነት
    ንቁ!—2017
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2025
wp25 ቁጥር 1 ገጽ 4-5
ሥዕሎች፦ 1. አንድ ወታደር ከታንክ ፊት ፊት ሲሄድ። 2. ጦርነት ተጽዕኖ ያሳደረባቸው የተለያየ ዘር ያላቸው ወንዶች፣ ሴቶችና ልጆች።

ጦርነት እና ግጭት ሁላችንንም የሚነካን እንዴት ነው?

“ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ በዓለም ላይ የአሁኑን ያህል ግጭት በዝቶ አያውቅም። ሁለት ቢሊዮን ሰዎች ማለትም ከዓለም ሕዝብ መካከል ሩብ ያህሉ የሚኖሩት እንዲህ ያለ ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች ነው።”

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ምክትል ዋና ጸሐፊ አሚና መሐመድ ጥር 26, 2023

በአሁኑ ወቅት ሰላም ባለባቸው አካባቢዎችም ጦርነትና ግጭት በድንገት ሊከሰት ይችላል። ዓለማችን ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ እንደ አንድ መንደር ስለሆነች ጦርነት ካለበት አካባቢ ርቀው የሚኖሩ ሰዎችም እንኳ መዘዙ ሊነካቸው ይችላል። ደግሞም ጦርነት የሚያስከትለው ጉዳት ውጊያው ካበቃ በኋላም ለረጅም ጊዜ ይቀጥላል። አንዳንድ ምሳሌዎችን እስቲ እንመልከት፦

  • ባዶ ሳህን የያዘ እጅ ምስል።

    የምግብ እጥረት። የዓለም የምግብ ፕሮግራም እንደገለጸው “አሁንም የረሃብ ትልቁ መንስኤ ጦርነት ነው። በዓለም ላይ ካሉት በረሃብ የተጠቁ ሰዎች መካከል 70 በመቶዎቹ የሚኖሩት በጦርነትና በዓመፅ በሚታመሱ አካባቢዎች ነው።”

  • ፊቷን በእጆቿ የሸፈነች በሐዘን የተዋጠች ሴት ምስል።

    አካላዊና አእምሯዊ ሕመም። ሰዎች ጦርነት በማንዣበቡ የተነሳ የሚሰማቸው ስጋት ለጭንቀትና ለውጥረት ሊዳርጋቸው ይችላል። በጦርነት ቀጠና ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ለአካላዊ ጉዳት ብቻ ሳይሆን ለአእምሯዊ ሕመም የመጋለጣቸው አጋጣሚም ሰፊ ነው። የሚያሳዝነው ደግሞ እንዲህ ባለው ሁኔታ ውስጥ የሕክምና እርዳታ ማግኘት አስቸጋሪ ነው።

  • ንብረቶቻቸውን በትልቅ መያዣ ሸክፈው የሚሄዱ ቤተሰብ ምስል።

    ስደት። የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር እንደገለጸው እስከ መስከረም 2023 ድረስ በዓለም ዙሪያ ከ114 ሚሊዮን የሚበልጡ ሰዎች ከመኖሪያቸው ተፈናቅለዋል። ለዚህ ችግር ዋነኛው መንስኤ ጦርነትና ግጭት ነው።

  • ከድሃ ጎጇቸው አጠገብ የቆሙ ቤተሰብ ምስል።

    የኢኮኖሚ ችግር። ጦርነት ብዙውን ጊዜ እንደ ዋጋ ግሽበት ያሉ የኢኮኖሚ ችግሮችን ያስከትላል። እንደ ሕክምናና ትምህርት ያሉ አገልግሎቶችን ለማሟላት ይውል የነበረው የመንግሥት ገንዘብ ጦርነትን ለመደገፍ መዋሉ ሰዎችን ለችግር ሊዳርግ ይችላል። ከዚህም ሌላ፣ በጦርነት የወደመውን ንብረት መልሶ ለመገንባት የሚያስፈልገው ገንዘብ በጣም ብዙ ነው።

  • ነዳጅ ሲፈስስ የሚያሳይ ምስል።

    ሥነ ምህዳራዊ ችግሮች። ሰዎች፣ የሚገለገሉበት የተፈጥሮ ሀብት ሆን ተብሎ ሲወድም ለመከራ ይዳረጋሉ። የውኃ፣ የአየርና የአፈር ብክለት ዘላቂ የጤና እክሎችን ሊያስከትል ይችላል። የተቀበሩ ፈንጂዎች የሚያስከትሉት አደጋም ውጊያው ካበቃ ከረጅም ጊዜ በኋላም ይቀጥላል።

በእርግጥም ጦርነት አውዳሚና አክሳሪ ነው።

ጦርነት እና የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢት

የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢት እንደሚገልጸው “የዚህ ሥርዓት መደምደሚያ” ምልክት ጦርነትንና ግጭትን ያካትታል። (ማቴዎስ 24:3) ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ የሚል ትንቢት ተናግሯል፦

  • “ጦርነትና የጦርነት ወሬ ትሰማላችሁ። . . . ሕዝብ በሕዝብ ላይ፣ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሳልና።”—ማቴዎስ 24:6, 7

  • “ስለ ጦርነትና ብጥብጥ ስትሰሙ አትሸበሩ።”—ሉቃስ 21:9

    እዚህ ጥቅስ ላይ የገባው “ብጥብጥ” የሚለው ቃል ረብሻን፣ ዓመፅን፣ በባለ ሥልጣናት ላይ የሚነሳን ተቃውሞ፣ መፈንቅለ መንግሥትን፣ ፖለቲካዊ ነውጥንና ሁከትን ሊያመለክት ይችላል።

ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት “‘የመጨረሻዎቹ ቀናት’ ወይም ‘የመጨረሻው ዘመን’ ምልክት ምንድን ነው?” የሚለውን ርዕስ jw.org ላይ አንብብ።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ