ተጨማሪ ሐሳብ
^ [1] (አንቀጽ 3) አንዳንድ የእምነት ባልንጀሮቻችን፣ ከባድ ሕመምን የመሳሰሉ ከአቅማቸው በላይ የሆኑ ችግሮች ስላሉባቸው አዘውትረው በስብሰባዎች ላይ መገኘት አይችሉም። እነዚህ ክርስቲያኖች ይሖዋ ሁኔታቸውን እንደሚረዳላቸውና በሙሉ ነፍስ የሚያቀርቡትን አምልኮ ከፍ አድርጎ እንደሚመለከተው እርግጠኛ መሆን ይችላሉ። ሽማግሌዎች፣ አቅማቸው ውስን የሆነው እነዚህ ክርስቲያኖች በስብሰባዎች ላይ ከሚቀርቡት መንፈሳዊ ፕሮግራሞች እንዲጠቀሙ ለመርዳት ዝግጅት ሊያደርጉ ይችላሉ፤ ለምሳሌ፣ ስብሰባውን በስልክ እንዲከታተሉ ወይም ተቀድቶ እንዲያዳምጡት ማድረግ ይቻላል።