የግርጌ ማስታወሻ
a እዚህ ላይ የሰፈረው ማብራሪያ መጽሐፍ ቅዱስ ፖርኒያ ወይም ዝሙት ብሎ በሚጠራው ርዕሰ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ይሆናል። (1 ቆሮንቶስ 6:9፤ ከዘሌዋውያን 18:6-22 ጋር አወዳድር።) ይህ ከሥነ ምግባር ውጪ የሆነውን ሁሉንም ዓይነት የጾታ ግንኙነት ያጠቃልላል። ኀፍረተ ሥጋን ማሳየት፣ የሌሎችን ኀፍረተ ሥጋ በማየት ወሲባዊ እርካታ ለማግኘት መሞከር፣ ወሲባዊ ጽሑፎችንና ሥዕሎችን ማሳየትና እነዚህን የመሳሰሉ ሌሎች ጸያፍ ድርጊቶች ፖርኒያ ባይሆኑም እንኳ የሕፃናትን ስሜት ሊጎዱ ይችላሉ።