የግርጌ ማስታወሻ
b ባለ ትዳር ሴቶች ተገደው የሚደፈሩት አንድ ባል ሚስቱን በጉልበት አሸንፎ አለፈቃዷ የፆታ ግንኙነት ሲፈጽም ነው። አንዳንድ ባሎች ሐዋርያው ጳውሎስ ባል በሚስቱ አካል ላይ አለው ብሎ የጠቀሰው “ሥልጣን” አንጻራዊ ሳይሆን ፍጹም ሥልጣን እንደሆነ አድርገው ያስቡ ይሆናል። ይሁን እንጂ ጳውሎስ “እንዲሁም ባሎች ደግሞ እንደ ገዛ ሥጋቸው አድርገው የገዛ ሚስቶቻቸውን ሊወዱአቸው ይገባቸዋል” ብሏል። ሐዋርያው ጴጥሮስም ባሎች ሚስቶቻቸውን “እንደ ደካማ ዕቃ አድርገው ለሴትነት ባሕርያቸው ሊጠነቀቁላቸው” እንደሚገባ ተናግሯል። አስገድዶ ወይም በኃይል ተጠቅሞ የፆታ ግንኙነት ለማድረግ የሚያስችል አንድም ቅዱስ ጽሑፋዊ ምክንያት የለም። — 1 ቆሮንቶስ 7:3–5፤ ኤፌሶን 5:25, 28, 29፤ 1 ጴጥሮስ 3:7 አዓት፤ ቆላስይስ 3:5, 6፤ 1 ተሰሎንቄ 4:3–7