የግርጌ ማስታወሻ
a የይሖዋ ምሥክሮች የኢየሱስን ዳግም ምጽአት በጣም በመናፈቃቸው ምክንያት ኢየሱስ ስለሚመጣበት ጊዜ ስህተት ሆነው የተገኙ ቀኖችን ተናግረዋል። በዚህም ምክንያት አንዳንድ ሰዎች ሐሰተኛ ነቢያት ናቸው ይሏቸዋል። ይሁን እንጂ አንድም ጊዜ ቢሆን የተነበይነው ‘በይሖዋ ስም’ ነው ብለው አያውቁም። ‘ይህ የይሖዋ ቃል ነው’ ብለው አያውቁም። የይሖዋ ምሥክሮች ኦፊሴላዊ መጽሔት የሆነው መጠበቂያ ግንብ “ትንቢት የመናገር ስጦታ የለንም።” (ጥር 1883 ገጽ 425) “ጽሑፎቻችንም ቅዱስ ናቸው ወይም ስህተት ሊኖርባቸው አይችልም አንልም” ብሎ ነበር። (ታኅሣሥ 15, 1896 ገጽ 306) በተጨማሪም መጠበቂያ ግንብ አንዳንዶች የይሖዋ መንፈስ ያላቸው በመሆናቸው “በአሁኑ ጊዜ የይሖዋ ምሥክሮች ሆነው በማገልገል ላይ የሚገኙ ሁሉ በመንፈስ ተነድተው ይናገራሉ ማለት አይደለም። በዚህ በመጠበቂያ ግንብ የሚወጡት ጽሑፎች በመንፈስ አነሣሽነት የተጻፉ፣ ስህተት የሌለባቸውና ስህተትም ሊገኝባቸው የማይችሉ አይደሉም” ብሏል። (ግንቦት 15, 1947 ገጽ 157) “መጠበቂያ ግንብ የሚያወጣቸው ጽሑፎች በመንፈስ መሪነት የተጻፉ ናቸው ወይም ቀኖና ናቸው አይልም።” (ነሐሴ 15, 1950 ገጽ 263) “እነዚህን ጽሑፎች የሚያዘጋጁት ወንድሞች የማይሳሳቱ አይደሉም። ጽሑፎቻቸውም እንደ ጳውሎስና እንደ ሌሎቹ የመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊዎች በመንፈስ የተጻፉ አይደሉም። (2 ጢሞ. 3:16) ስለዚህ ይበልጥ ግልጽ የሆነ ማስተዋል በተገኘ ቁጥር አንዳንድ አመለካከቶችን ማስተካከል አስፈላጊ ሆኗል። (ምሳሌ 4:18)”—የካቲት 15, 1981 ገጽ 19