የግርጌ ማስታወሻ
c ሰዎች በአጠቃላይ ወሲባዊ ሐሳቦችን በማውጠንጠን የሚያሳልፉት ጊዜ ሌሎች ሐሳቦችን ከሚያውጠነጥኑበት ጊዜ ጋር ሲወዳደር በጣም አነስተኛ እንደሆነ ጥናቶች ይጠቁማሉ። ሆኖም በዶክተር ኤሪክ ክሊንገር የተዘጋጀው ዴይድሪሚንግ የተባለው መጽሐፍ እንዲህ ይላል:- “ስሜታችንን ያነሳሱ ነገሮች ይበልጥ ጉልህ ሆነው ይታወሱናል። ወሲባዊ ሐሳቦችን ማውጠንጠን የጾታ ፍላጎት ስለሚቀሰቅስ ብዙውን ጊዜ ከሌሎች ሐሳቦች ይልቅ የምናስታውሰው ወሲባዊ ሐሳቦችን ነው።”