የግርጌ ማስታወሻ
a አንድ ልጅ በጾታ ተነወረ የሚባለው አንድ ሰው የራሱን የጾታ ፍላጎት ለማርካት ልጁን መሣሪያ አድርጎ በሚጠቀምበት ጊዜ ነው። ይህ ድርጊት ብዙውን ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ ዝሙት ወይም ፖርኒያ ብሎ የሚጠራውን ድርጊት ይጨምራል፤ ይህም የጾታ ብልትን ማሻሸትን፣ የጾታ ግንኙነት መፈጸምንና በአፍ ወይም ደግሞ በፊንጢጣ መገናኘትን ሊጨምር ይችላል። ጡትን መደባበስ፣ ከሥነ ምግባር ውጭ የሆነ ድርጊት ለመፈጸም መጠየቅ፣ ዕርቃነ ሥጋን የሚያሳዩ የብልግና ጽሑፎች ለልጅ ማሳየት፣ ተደብቆ የሰውን ዕርቃነ ሥጋ ማየት ወይም ሰዎች የጾታ ግንኙነት ሲፈጽሙ መመልከትና ሆን ብሎ ዕርቃነ ሥጋን ማሳየት የመሳሰሉት አስነዋሪ ድርጊቶች መጽሐፍ ቅዱስ “ነውር” ብሎ ከሚያወግዘው ነገር ጋር የሚወዳደሩ ሊሆኑ ይችላሉ።—ገላትያ 5:19-21 NW፤ በመጋቢት 15, 1983 የእንግሊዝኛ መጠበቂያ ግንብ ገጽ 30 ላይ ያለውን የግርጌ ማስታወሻ ተመልከት።