የግርጌ ማስታወሻ
a እርግጥ፣ ሐዋርያው ጳውሎስ ክርስቲያኖች ‘በኋላቸው ያለውን እንዲረሱ’ ምክር ሰጥቷል። ሆኖም ጳውሎስ እዚህ ላይ እየተናገረ ያለው ቀደም ሲል ስለነበረው ክብርና ዓለማዊ ስኬት ነው፤ በኋላ ግን ይህን “እንደ ጉድፍ” ቆጥሮታል። ቀደም ሲል የደረሰበትንና በግልጽ የዘረዘረውን መከራ አስመልክቶ መናገሩ አልነበረም።—ፊልጵስዩስ 3:4-6, 8, 13፤ ከ2 ቆሮንቶስ 11:23-27 ጋር አወዳድር።