የግርጌ ማስታወሻ
a በኤድስ እንደተያዘ የሚያውቅ አንድ ሰው የይሖዋ ምሥክር ለመሆንና ለመጠመቅ በሚፈልግበት ጊዜ ምን ማድረግ ይኖርበታል? ኤድስ የመዋኛ ገንዳዎችን በጋራ በመጠቀም እንደተጋባ የሚያመለክት ማስረጃ እስከ አሁን ያልተገኘ ቢሆንም ለሌሎች ስሜት በማሰብ ብቻውን እንዲጠመቅ ቢጠይቅ ጥሩ ይሆናል። በመጀመሪያው መቶ ዘመን የነበሩ ብዙ ክርስቲያኖች ሕዝብ በተሰበሰበባቸው ቦታዎች የተጠመቁ ቢሆንም በተለያዩ ሁኔታዎች ምክንያት ብቻቸውን የተጠመቁም ነበሩ። (ሥራ 2:38–41፤ 8:34–38፤ 9:17, 18) ሌላው አማራጭ ደግሞ በኤድስ የተያዘው ሰው መጨረሻ ላይ እንዲጠመቅ ማድረግ ይሆናል።