የግርጌ ማስታወሻ
a ቅዱሳን ጽሑፎችን በማጣመም እነዚህን እገዳዎች የሚደግፉ ሐሳቦች ለማግኘት ተሞክሮ ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ያለ ነገር ባይናገርም ሰፊ ተደማጭነት የነበረው የሃይማኖት ምሁሩ ተርቱሊያን፣ ሴት ልጅ “ለመጀመሪያው ኃጢአትና ለሰው ልጅ ኩነኔ” መንስዔ በመሆኗ ሴቶች “እንደ ሔዋን በሐዘን እየተደቆሱና እየተጸጸቱ” መኖር አለባቸው ሲል አስተምሯል። እንዲያውም በተፈጥሮ ቆንጆ የሆነች ሴት ውበቷን መደበቅ አለባት እስከ ማለት ደርሶ ነበር።—ከሮሜ 5:12–14፤ 1 ጢሞቴዎስ 2:13, 14 ጋር አወዳድር።